DW

የዓለም ዜና

News AM ↓ 100 episodes

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።

Author

DW

Category

News

Podcast website

www.dw.com

Latest episode

Jul 10, 2026

Where to listen?

Podcasts in the app Replaio Radio Coming soon

Podcasts are coming to the app soon. Install now and be the first to see a whole new take on podcasts

Get it on Google Play Install for free Android 5M+ downloads · 4.8 rating iOS soon

Episodes

DW Amharic የሰኔ 08 ቀን 2018 የዓለም ዜና 15.06.2026

ከደሴ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ የሕዝብ ማጓጓዣ አውቶቡስ 170 ሜትር ርዝመት ያለው ገደል ውስጥ በመውደቁ የ31 ሰዎች ሲሞቱ 30 ሰዎች ከባድና ቀላል ጉዳት ደረሰባቸው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከቢሾፍቱ አቅራቢያ እየተገነባ በሚገኘው አውሮፕላን ማረፊያ ምክንያት “የሚጎዳ አርሶ አደር” እንደማይኖር ቃል ገቡ። የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽነር ፎልከር ቱርክ በሱዳን ጦርነት የድሮን አጠቃቀም ላይ የታየውን “ከፍተኛ ጭማሪ” አወገዙ። ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን የገጠሙትን ጦርነት ለማብቃት ከሥምምነት መድረሳቸውን አሳወቁ። ሩሲያ በዩክሬን ከተሞች ላይ በሚሳይሎች በፈጸመችው ጥቃት11 ሰዎች ተገደሉ።

የሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና 14.06.2026

የሶማሊላንድ ፕሬዝደንት አብዲራሕማን ሞሐመድ አብዱላሒ "ታሪካዊ" የተባለለትን ጉብኝት እውቅና በሰጠቻቸው ሀገር እስራኤል እያደረጉ ነው። በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብቻ ከ 700 በላይ ሰዎች በኢቦላ ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ። የእስራኤል ጦር ዛሬ የሂዝቦላህ ቡድንን ለማጥቃት የሊባኖስ ዋና ከተማ ቤይሩት ደቡባዊ ክፍልን ከአየር ደበደበ። ቡድኑ አስቀድሞ ዛሬ ጠዋት በሰሜናዊ እስራኤል የድሮን ጥቃት ፈፅሟል። የኢራን ዋና ተደራዳሪ ሞሐመድ ባግኸር ጋሊባፍ በዚህ አይነት ሁኔታ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር የሰላም ድርድሩን መቀጠል ፋይዳ እንደማይኖረው ተናገሩ።

የሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና 13.06.2026

• የኤርትራው የማስታወቂያ ሚንስትር የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ብልጽግና ፓርቲ በተዛባ መረጃ ላይ የተመሰረተ ፕሮፖጋንዳ ያሰራጫል ሲሉ ከሰሱ ። • በኢራን እየተካሄደ ያለው ጦርነት የአውሮፕላን ነዳጅ ዋጋን በመናርና የአቅርቦት እጥረትን በመፍጠር በአፍሪካ አየር መንገዶች ላይ ከፍተኛ ቀውስ እየደቀነ መሆኑን የአፍሪካ አየር መንገዶች ማኅበር (AFRAA) አስጠነቀቀ። • ዩጋንዳ በኤቦላ ወረርሽኝ ምክንያት በአሜሪካ እና በሌሎች ሀገራት የተጣለባትን የአየር ጉዞ እገዳ «ኢ-ፍትሐዊ» ስትል ኮነነች። • የኒጀር ወታደራዊ ሁንታ ግብረ-ሰዶማዊነትን በወንጀል የሚቀጣ አዲስ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ማውጣቱን አስታወቀ።

የሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና 12.06.2026

በአፍሪቃ ሕብረት የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ተወካይ የተመራ የልዑካን ቡድን ወደ መቀለ መጓዙ ተሰማ። የቡድኑ መሪ የጉዟቸው ዓላማ ሁኔታዎች እንዳይባባሱ አስቀድሞ ለማርገብ ነው ብለዋል። የትግራይ ክልል ባለሥልጣናት ለዳግም ጦርነት እየተዘጋጁ ነው መባሉን ውድቅ ማድረጋቸው ተዘገበ። «ላ ክሯ» ለተሰኘ ጋዜጣ የምትዘግብ ፈረንሳዊት ጋዜጠኛ ከኢትዮጵያ መባረሯን ድርጅቱ አመለከተ። የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን አሾልካ አወጣች ያሉት የስምምነት በጽሑፍ ያለውን ውል የሚወክል አይደለም አሉ። የኢራን ባለሥልጣናት በበኩላቸው ጣላቶቻችን ያሏቸው አሜሪካን እና እስራኤል ከኃይል በቀር የድርድር ቋንቋ አይገባቸውም ብለዋል።

የሐሙስ ሰኔ 4 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና 11.06.2026

መቐለ፥ ደብረፅዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር) ኦሉሴጉን ኦባሳንጆን ዛሬ መቐለ ከተማ ዉስጥ ተቀብለው አነጋገሩ፤ አ.አ፥ ለ2019 ዓ.ም የበጀት ዓመት ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ለፕላን-በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተመራ፤ ጂዳ፥ ሣዑዲ ዓረቢያ ታስረው የነበሩ 1,655 ኢትዮጵያውያን ምሕረት አገኙ፤ የአሜሪካ ጦር በሁለተኛው ቀን ኢራን ውስጥ በርካታ ኢላማዎችን እየመታ መሆኑን ዐሳወቀ፤ ኬፕታውን፥ የኬፕ ታውን ማራቶን ከዓለማችን ታላላቅ የማራቶን ውድድሮች መካከል አንዱ ኾነ፤ ሜክሲኮ ሲቲ፥ የዓለም እግር ኳስ ጨዋታ በደቡብ አፍሪቃ እና በሜክሲኮ መካከል ዛሬ ማታ ይከፈታል

የሰኔ 3 ቀን፣ 2018 የዓለም ዜና 10.06.2026

-ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክና ዩጋንዳ ዉስጥ የተሰራጨዉ የኢቦላ ተሕዋሲ የያዛቸዉ ሰዎች ቁጥር 620 ደረሰ።ተሕዋሲዉ 120 ያክል ሰዎች መግደሉ ተረጋግጧል።ሶስት የኮንጎ ቤተ-ምርመራዎች ተሕዋሲዉን መመርመሪያ መሳሪያና ንጥረ-ነገር አልቆባቸዋል።---ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን እንዳዲስ መደባደብና መዛዛት ይዘዋል።የዩናይትድ ስቴትስ ጦር የኢራን ወታደራዊ ተቋማት ያላቸዉን ሥፍራዎች ሲደበድብ፣ ኢራን ባፀፋዉ ከባሕሬን እስከ ዮርዳኖስ የሚገኙ የዩናይትድ ስቴትስ የጦር ሠፈሮችን ደብድባለች።----ዩናይትድ ስቴትስ እንዳይገባ የተከለከለዉ ሶማሊያዊ ዓለም አቀፍ የእግር ኳስ ግጥሚያ ዳኛ ሞቃዲሾ ሲመለስ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት።

የዓለም ዜና፤ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ማክሰኞ 09.06.2026

አርስተ ዜና--በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የተፈናቃዮች ልዩ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በአማራ ክልል ዛሬ ተከናወነ። ከኦሮሚያ ክልል ምስራቅና ምዕራብ ወለጋ እንዲሁም በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል በነበሩ የፀጥታ ችግር ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸዉ እንዲመለሱ ጠይቀዋል።-በኢትዮጵያ ፌደራል መንግስትና በህወሓት መካከል ተባብሶ እንደቀጠለ የተገለፀውን ውጥረት በተመለከተ፣ የፕሪቶሪያውን ግጭት በዘላቂነት የማቆም የሰላሞ ስምምነት በዋነኛነት ከመራው የአፍሪቃ ኅብረት በኩል እስካሁን የወጣ መግለጫም ይሁን የተሰጠ አስተያያት የለም።-የዓለም ዋንጫ ጨዋታን ለመምራት ለሀገሩ የመጀመሪያው ለመሆን የተዘጋጀው ሶማሊያዊ ዳኛ ወደ አሜሪካ እንዳይገባ ተከለከለ።

የሰኞ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና 08.06.2026

የደቡብ አፍሪቃው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ደቡብ አፍሪቃ በሚገኙ ስደተኞች ላይ ከሕግ በላይ ሆነው እርምጃ የሚወስዱትንሰዎች ባለሥልጣናቶቻቸውእንደማይታገሱ አሳሰቡ ። ኢራን እስራኤልን ትናንትናና ዛሬ ስትደበድ እሥራኤልም በአጸፋው ኢራንን ዛሬ መታለች ። ትናንት ወደ እሥራኤል ሮኬቶችን በተመተኮስ ማጥቃት የጀመረችው ኢራን 24 ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የመከላከል ዘመቻውን እንደምታቆም አስታውቃለች። ከእሁዱ የኢራን ጥቃት በኋላ የእሥራኤል ጦር ዛሬ (መጠነ ሰፊ) ያለውን ጥቃት በኢራን ላይ መፈጸሙን ገልጿል። ማልታ አቅራቢያ በሰጠመች ጀልባ ውስጥ የነበሩ ቢያንስ 11 ስደተኞች ሞቱ። ወደ 50 የሚሆኑ ደግሞ ተረፉ።

የግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና 07.06.2026

የማዕከላይ አፍሪካ ሪፐብሊክ መንግስት ከአሜሪካ የሚጠረዙ ስደተኞችን ተቀብሎ ለማስተናገድ መስማማቱን ከሐገሪቱ የወጡ ዲፕሎማሲያዊ ምንጮች አረጋገጡ። ዩናይትድስቴትስና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱት ጦርነት ዛሬ 100 ቀናትን ደፍኗል። ዩናይትድ ስቴትስ በተለያዩ ባንኮች ታግዶ የሚገኘውን የኢራን ሐብት፤ በኢራን የሚሳይልና የድሮን ጥቃት ለደረሰባቸው የባህረ ሰላጤ ሀገራት እንዲውል ማቀዷን አስታወቀች።

DW Amharic-የቅዳሜ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና 06.06.2026

የዛሬው የዓለም ዜና ፣የኢትዮጵያ አየር ሃይል በትግራይ ክልል ሸራሮ ከተማ አቅራቢያ አካሄደው በተባለው የድሮን ጥቃት ጉዳት ደረሰ መባሉን።ናይጄሪያ እና ጋና ዜጎቻቸው ደቡብ አፍሪካን ለቀው እንዲወጡ ሀሳብ ማቅረባቸውን፣ኩዌት፤ አዲሱ የኢራን ጥቃት 'አደጋ የሚያባብስ ' መሆኑን መግለጿን።በጀርመን በፖለቲካዊ መነሻ የሚፈጸም ወንጀል በከፍተኛ ደረጃ ጨምሯል መባሉን፣የሮማው ሊቃነ ጳጳስ በዓለም ላይ ዋልታረገጥነ አስተሳሰብ እንዲያበቃ ጥሪ ማቅረባቸውን እንዲሁም ኢራን ቅዳሜ ዕለት ቱርክን ለቀው ወደ ሜክሲኮ ከሚያመሩት ተጫዋቾቿ ጋር ለሚጓዙት የዓለም ዋንጫ ቡድን የድጋፍ ሰራተኞች ቪዛ በመከልከሏ አሜሪካን ክፉኛ መቸቷን አካቷe።

የዓለም ዜና፤ ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም አርብ 05.06.2026

አርስተ ዜና-አሜሪካ በኩባ ላይ ተጨማሪ ማዕቀብ አሳረፈች። --ቅድሚያ ለሰብአዊ መብት የተባለ አገር በቀል የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት ዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ በትግራይ እየተካሄደ ነው ባለው አስገዳጅ ወታደራዊ ምልመላን እንዲያወግዝ እና እንዲያስቆም ጥሪ አቀረበ።--በደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በቡርጂ እና ጌዴኦ ዞኖች ምርጫ ሲያጭበረብሩ የተገኙ ከስድስት እስከ አሥር ወር እሥራት ተቀጡ ፡፡--የቀድሞ የአዲስ አበባን ከንቲ አምባሳደር ዓሊ አብዶ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።--የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ከአራት ዓመታት በላይ የዘለቀው ጦርነት እንዲያበቃ ስምምነት ላይ ለመድረስ ለፑቲን ግልፅ ደብዳቤ ፃፉ።

የግንቦት 27 ቀን 2018፤ ዓለም ዜና 04.06.2026

በዛሬው የዓለም ዜና ተቃዋሚው የቁጫ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በክልሉ ምርጫ«የማጭበርበር ተግባራት ተፈጽሟል» ሲል ቅሬታ ማቅረቡን።የምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ)በሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ የተከሰተዉ ሁከት በጥልቅ እንዳሳሰበው ማስታወቁ።በዓለም ላይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች ችላ ተብለዋል ሲል አንድ የእርዳታ ድርጅት መግለጹን።ሊባኖስ፤ የእስራኤል የድሮን ጥቃቶች መቀጠላቸውን መግለጿ።ኩዌት የኢራን ድሮን አውሮፕላን ማረፊያዋን መምታቱን ማስታወቋን።የአሜሪካ ሕግ አውጪዎች ሀገሪቱ በኢራን የምታደርገውን ወታደራዊ እርምጃ ለማስቆም የቀረበውን ውሳኔ መደገፋቸውን የሚያስቃኙ ዜናዎች የሚሉት ተካተዋል።

የግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና 03.06.2026

የግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን እየሰፋ መጣ ያሉትን ጥቃት የመንግሥት የፀጥታ አካላት ያላቸውን መዋቅር ተጠቅመው እንዲያስቆሙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያርክ ጠየቁ። በኢትዮጵያ የአውሮጳ ኅብረት ልዑክ እና በአዲስ አበባ የሚገኙ የኅብረቱ አባል ሃገራት ኤምባሲዎች ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ምርጫ ያልተካሔደባቸው የምርጫ ክልሎች ድምፅ የመስጠት «ዕድል ይሰጣቸዋል» የሚል ተስፋ እንዳላቸው አስታወቁ። ዴሞክራቲክ ኮንጎ ውስጥ በኢቦላ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር 343 ደረሰ። ኢራን በመካከለኛው ምሥራቅ በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት ቀጥላለች።

የዓለም ዜና፤ ግንቦት 25 ቀን 2018 ማክሰኞ 02.06.2026

-አርሰተ ዜናዎች--ሩሲያ በዩክሬን ላይ በድጋሚ በሰነዘረችዉ ከፍተኛ ጥቃት ቢያንስ አስር ሰዎች ተገደሉ ከ100 በላይ ሰዎች ደግሞ ቆሰሉ።-በኢትዮጵያ የተካሄደው የሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫ የድምፅ ቆጠራ ውጤት፣ በምርጫ ጣቢያዎች እየተለጠፈ ይገኛል።--በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ሀገረ ስብከት በአስኮ ወረዳ በሺርካ ወረዳና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 13 ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያኖች መገደላቸውን ሀገር ስብከቱ አመለከተ። የመቶ አንድ ዓመት እድሜ እንደነበረው የተገለጸው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያንም ሙሉ በሙሉ በእሳት መጋየቱ ተነግሯል።

DW Amharic የግንቦት 23 ቀን 2018 የዓለም ዜና 31.05.2026

የጋምቤላ ክልል ፖሊስ “የተለየ የይለፍ ፈቃድ ካልተሰጠ በቀር” ማንኛውም ተሽከርካሪ ከዛሬ ጀምሮ ለሦስት ቀናት መንቀሳቀስ እንደማይችል አስታወቀ። በምሥራቃዊ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አምስት ሕሙማን ከኢቦላ ማገገማቸውን የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴድሮስ አድኃኖም ተናገሩ። ኢራን ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው ድርድር የኑክሌር የጦር መሣሪያ ላለመስራት መስማማቷን የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጹ። የኢራን ዋና ተደራዳሪ ሞሐመድ ባግኸር ጋሊባፍ ግን “የኢራናውያን መብቶች መከበራቸውን ሳናረጋግጥ አንዳች ሥምምነት አናጸድቅም” ብለዋል።

የግንቦት 22 ቀን 2018 ፤የዓለም ዜና 30.05.2026

የዛሬው የዓለም ዜና፤የአማራ ፋኖ የጣለው የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ገደብ የምርጫ ሥራዉን ስለማስተጎጎሉ የደረሰው መረጃ እንደሌለ ምርጫ ቤርድ ማስታወቁ፣የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር የኢቦላ ወረርሽን ወደተቀሰቀሰባት ዲሞክራቲክ ኮንጎ ማምራታቸውን፣ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ ነዋሪዎች አካባቢውን እንዲለቁ ትዕዛዝ መስጠቷን፣ በጀርመን የሙኒክ አውሮፕላን ማረፊያ አጠራጣሪ ድሮን መታየቱን ተከትሎ ለአጭር ጊዜ በረራ መቋረጡን አሜሪካ ስምምነት ላይ ካልደረሰ በኢራን ጦርነቱን እንደገና ለመጀመር ዝግጁ መሆኗን መግለጿን፣እንዲሁምሩሲያ፤ በአርሜኒያ የሚገኙ አምሳደሯን መጥራቷን አካቷል።

የግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና 29.05.2026

ከአማራ ክልል መንገደኞችን ጭኖ ትናንት ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ አውቶብስ ላይ በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት በርካቶች መገደላቸው ተሰማ። ማዕከላዊ ኬንያ ውስጥ በሚገኘው የሴቶች አዳሪ ትምህርት ቤት የተነሳውን እሳት በመለኮስ የተጠረጠሩ ስምንት ተማሪዎች መያዛቸውን ፖሊስ አስታወቀ። የኬንያ ፍርድ ቤት በሀገሪቱ በኤቦላ ተሐዋሲ ለተያዙ የአሜሪካ ዜጎች አግልሎ ማቆያ የማዘጋጀት እቅድን በጊዜያዊነት አገደ። ኢራን ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ለገባችበት ውዝግብ ለታሰበው የሰላም ስምምነት ከቃል ይልቅ ተግባር እንደምትፈልግ አስታወቀች።

DW Amharic የግንቦት 20 ቀን 2018 የዓለም ዜና 28.05.2026

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ በጥሞና ወቅት “ፕሮጀክት ማስጀመር እና ማስመረቅ” ከለከለ። ክልከላው የምርጫውን ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ያግዛል በተባለው የጥሞና ጊዜ ከማይደረጉ እንቅስቃሴዎች ውስጥ የተካተተ ነው። ከኢትዮጵያ መንግሥት የሚዋጋው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ከነገ ጀምሮ በአማራ ክልል “ለተከታታይ አምስት ቀናት ከአንቡላንሶች በስተቀር ሁሉም መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ መደረጋቸውን” አስታወቀ። የኢትዮጵያ መንግሥት አገሪቱ አንድ ቢሊዮን ዶላር የተበደረችበት ቦንድ ባለቤቶችን ከሚወክል ጊዜያዊ ኮሚቴ ጋር ያደረገው ውይይት ውጤታማ ሳይሆን መቅረቱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የረቡዕ ግንቦት 19 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና 27.05.2026

አ.አ፥ ለቀጣዩ ምርጫ ሥራ ዝግ እንደሚኾን ምርጫ ቦርድ ዐሳወቀ፤ አ.አ፥ 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በመላ ኢትዮጵያ ተከበረ፤ ጆሐንስበርግ፥ የጋና መንግሥት ዜጎቹን መጤ ጠል ሥጋት ካጠላባት ደቡብ አፍሪቃ ወደ አገራቸው እየመለሰ ነው፤ ዋሽንግተን፥ ካናዳ እና ባሐማ ከኤቦላ ጋር የተገናኘ የጉዞ ክልከላ ተግባራዊ አደረጉ፤ ናይሮቢ፥ ካናዳ እና ባሐማ ከኤቦላ ጋር የተገናኘ የጉዞ ክልከላ ተግባራዊ አደረጉ፤ ጋዛ፥እሥራኤል አዲስ የተሾሙ የሐማስ ወታደራዊ ክንፍ አዛዥን መግደሏን ዐሳወቀች፤

የግንቦት 18 ቀን 2018 ዓም የዓለም ዜና 26.05.2026

የግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና በሱዳኑ ጦርነት ከፈጥኖ ደራሹ ኃይል በምህጻሩ RSF ጎን ተሰልፈው የሚዋጉ ኮሎምብያውያን የግል ቅጥረኛ ወታደሮችን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ታሰለጥናለች ሲል ሂዩመን ራይትስ ዋች አስታወቀ ። በኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እጎ ዩጋንዳ ዉስጥ ተጨማሪ ሰዎች በኢቦላ ተሕዋሲ መያዛቸዉን የሁለቱ ሐገራት የጤና ባለሥልጣናት አስታወቁ። ኢራን፣ ዩናይትድ ስቴትስ ትናንት የፈጸመችባትን የአየር ድብደባ አወገዘች። ድብደባዎቹን የተኩስ አቁሙን የጣሰ ሲል ያወገዘው የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት፣ ጥቃቶቹ ለሚያስከትሉት መዘዞች ሁሉ ዋሽንግተን ሃላፊነቱን እንደምትወስድ አስጠንቅቋል።

የግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና 25.05.2026

መገናኛ ብዙኃን ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በመንግሥት ቁጥጥር ስር በሆነበት፤ አመጽና ዛቻን በመጋፈጥ፤ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በሚካሄደው ምርጫ እንደሚሳተፉ ተዘገበ። ዓለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ተልእኮ የወታደሮች ቁጥር በመቀሱ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን አንድ ጥናት አመለከቱ። ኢራን በመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነቱን ለማስቆም ከአሜሪካ ጋር የምታካሄደው ድርድር መሻሻሎች ቢኖሩትም ስምምነት ላይ ገና አልተደረሰም አለች። ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው ከኢራን ጋር የሚደረገው ስምምነት ወይ ታላቅና ትርጉም ያለው ይሆናል ወይ ደግሞ ስምምነት አይኖርም ብለዋል።

የግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና 24.05.2026

• በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የኢቦላ ወረርሽኝ የሟቾች ቁጥር 204 ደረሰ። ኢትዮጵያን ጨምሮ 10 የአፍሪካ ሀገራት ወረርሽኙ አስግቷቸዋል። • አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱን ለማቆም የሚያስችላቸው ስምምነት ላይ ለመድረስ መቃረባቸው ተሰማ። • ሩሲያ ዛሬ ሌሊት በዩክሬን መጠነ-ሰፊ የድሮን እና የሚሳኤል ጥቃት “ኦሬሽኒክ” የተሰኘውን የሃይፐርሶኒክ ባሊስቲክ ሚሳኤል • በፓኪስታን በደረሰ የአጥፍቶ ጠፊ የቦምብ ጥቃት የ23 ሰዎች ህይወት አለፈ። • ኢትዮጵያዉያን አትሌቶች ዛሬ ደቡብ አፍሪቃ ኬፕታውን ውስጥ የተደረገውን የማራቶን ሩጫ የቦታውን ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር አሸነፉ ።

የግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና 23.05.2026

ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎና ኡጋንዳ በተጨማሪ 10 የአፍሪካ ሐገራት የኢቦላ ቫይረስ ሥርጭት እንደሚያሰጋቸው የአፍሪካ የበሽታዎች መከላከያና መቆጣጠሪያ ድርጅት አስታወቀ። ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን ላይ ዳግም ጦርነት የምታውጅ ከሆነ ብርቱ አጸፋዊ ምላሽ እንደምትሰጥ ኢራን አስጠነቀቀች። በሰሜን ቻይና በምትገኝ የሻንዚ ግዛት በአንድ የከሰል ማዕድን ማውጫ ትላንት ባጋጠመ ፍንዳታ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ቢያንስ 90 መድረሱን ተሰማ። ዩክሬይን በሩስያ ቁጥጥር ሥር በሚገኘው እና የቀድሞ ግዛቷ በነበረው ሉጋንስክ ከተማ ፈጸመችው በተባለ የድሮን ጥቃት 18 ሰላማዊ ሰዎች ሲሞቱ 48 መቁሰላቸውን የአካባቢው የሩስያ ገዢ አስታወቁ።

የዓለም ዜና፤ ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም አርብ 22.05.2026

አርስተ ዜና -የደቡብ አፍሪቃ ባለስልጣናት ተባብሶ የቀጠለዉን ጥቁር የውጭ ዜጋ ጥላቻን ተከትሎ ጥቃትን በመፍራት ደርባን በሚገኘ አንድ የቤተክርስቲያን ማእከል ዉስጥ ከለላ የጠየቁ አፍሪቃዉያን ከማዕከሉ አስወጡ። ኢትዮጵያዉያንም ይገኙበታል።-ህንድና የአፍሪቃ ህብረት በሚቀጥለው ሳምንት በኒው ደልሂ ሊያካሂዱት የነበረው የመሪዎች ጉባዔ በኮንጎ በተቀሰቀሰዉ የኢቦላ ወረርሽኝ ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ ተራዘመ። -የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮ ፈረንሳይ በቅኝ ግዛቶቿ የነበረውን ባርነት ለመቆጣጠር ያገለገሉትን ያረጁ ህግጋቶች እንድታስወግድ እንደሚፈልጉ ተናገሩ። ሕግጋቱ አገራቸዉ ዛሬ ከምትላቸው እሴቶች ጋር አይጣጣሙም ብለዋል።

የግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና 21.05.2026

የግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ (ኦፌኮ) ለመንግሥት አቅርቦት የነበረው ጥያቄ አጥጋቢ ምላሽ ባለማግኘቱ በምርጫው ተሳትፎው እጅግ የተቀዛቀዘ እንዲሆን ማድረጉን አስታወቀ ። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የትምህርት ቢሮ በክልሉ የ2018 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ከታቀደው አንድ ወር ቀደም ብሎ እንደሚያበቃ አስታወቀ። ባለፉት 3 ሳምንታት ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ፣ ዩጋንዳ ወይም ደቡብ ሱዳን የነበሩ አሜሪካውያን ጠለቅ ላለ ምርመራ ፣በዋሽንግተን ዳላስ አውሮፕላን ማረፊያ በኩል ብቻ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ እንዲገቡ የአሜሪካን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳሰበ ።

Listen to the የዓለም ዜና podcast in Replaio

Radio and podcasts in one app - free, with no sign-up. Install today and do not miss the launch

Get it on Google Play

Replaio is not a podcast publisher; show names, artwork and audio belong to their authors and are distributed through public RSS feeds.