DW

የዓለም ዜና

News AM ↓ 100 episodes

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።

Author

DW

Category

News

Podcast website

www.dw.com

Latest episode

Jul 10, 2026

Where to listen?

Podcasts in the app Replaio Radio Coming soon

Podcasts are coming to the app soon. Install now and be the first to see a whole new take on podcasts

Get it on Google Play Install for free Android 5M+ downloads · 4.8 rating iOS soon

Episodes

የሐምሌ 3 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና 10.07.2026

የሐምሌ 3 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና ከዩናይትድ ስቴትስ ወደ ኢኩዋቶርያል ጊኒ የተጠረዙ ከኢትጵዮያ፣ከአንጎላ እና ከሞሪቴንያ መሆናቸው የተገለፀ 17 ስደተኞች በተያዙበት ሆቴል ውስጥ በኤቦላ እንደተያዘ የሚጠረጠር ቢያንስ አንድ ሰው ተገልሎ እንደሚገኝ የተጠራዦቹ ጠበቆች ተናገሩ። ማላዊ 38 ሺህ ዜጎቿን በአንድ ወር ውስጥ ከደቡብ አፍሪቃ ወደ ሀገራቸው መመለሷን ዛሬ አስታውቃለች። ስድስት የማላዊ ዜጎች መንገድ ላይ ታመው ሞተዋል። የጀርመን የእግር ኳስ ፌደሬሽን በምህጻሩ DFB ፕሬዝዳንት እና ምክትላቸው ለጀርመን ብሔራዊ ቡድን አስልጣኝነት ከታጩት ከዩርገን ክሎፕ ጋር ለመነጋገር ዛሬ ወደ ኒውዮርክ ተጓዙ።

የሐሙስ ሐምሌ 2 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና 09.07.2026

ናሜይ፥ ሩስያ እና የሣኅል ቀጠና አገራት ወታደራዊ ግንኙነታቸውን ሊያጠናክሩ ነው ፤ አንካራ፥ የኔቶ ጉባኤ በተሳታፊዎች ስምምነት ተጠናቀቀ፤ቤርሊን፥ ራኄ መንግሥት ፍሪደሪሽ ሜርስ ትናንት የተጠናቀቀው ኔቶ ጉባኤ ከጠበቁት በላይ መኾኑን ተናገሩ፤ ቴሕራን፥ ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በመካከለኛው ምሥራቅ ጥቃት እየተሰናዘሩ ነው፤ ማሽሐድ፥የቀድሞዉ የኢራን ላዕላይ መሪ አያቶላሕ ዓሊ ኻምኔይ ተቀበሩ፤ ሞሮኮ እና ፈረንሣይ ወደ ግማሽ ፍጻሜ ለማለፍ ፍልሚያ

የዓለም ዜና፤ ሐምሌ 01 ቀን 2018 ዓም ረቡዕ 08.07.2026

አርስተ ዜና፤ የደቡብ አፍሪቃ ፖሊስና ወታደራዊ ኃይል በጆሃንስበርግ አቅራቢያ በሕገ-ወጥ የማዕድን ቁፋሮ ሥራዎች ላይ ባደረጉት ከፍተኛ ዘመቻ ከ200 በላይ ሰዎችን አሰሩ። በደቡብ አፍሪቃ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን መካከል ህጋዊ ወረቅት የሌላቸዉ ስለመያዝ አለመያዛቸዉ እስካሁን የወጣ ግልፅ መረጃ የለም።-የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኔቶ ስብሰባ አንካራ ተገኝተዋል። ትራምፕ ድርጅቱ ባሳየዉን ወታደራዊ ኤግዚቢሽን የተደሰቱ አይመስልም። የአውሮጳ ህብረት ሀገራት ኔቶን ለማጠናከር የሚያደርጉትን ጥረትና የኢራን ጦርነት ለመቀላቀል ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ትራምፕ በተደጋጋሚ ተችተዋል።

የማክሰኞ ሰኔ 30 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና 07.07.2026

አ.አ፥ ጠ/ሚ ዐቢይ ስለ ሕገ መንግሥቱ ተናገሩ

DW Amharic የሰኔ 29 ቀን 2018 የዓለም ዜና 06.07.2026

የትግራይ ክልል ባለሥልጣናት የ15 ዓመት አዳጊዎችን ጨምሮ ሲቪል ሰዎችን እያፈኑ በግዳጅ ለውትድርና በመመልመል ላይ እንደሚገኙ ሒውማን ራይት ዎች ወነጀለ። በሱዳን እየተካሔደ በሚገኘው ጦርነት በስድስት ወራት ብቻ 330 ሕጻናት መገደላቸውን የተባበሩት መንግሥታት የሕጻናት መርጃ ድርጅት አስታወቀ። ሐማስ የጋዛን መንግሥታዊ መዋቅር መፍረሱን አስታወቀ። የዩክሬን ጦር ኦምስክ በተባለ ግዙፉ የሩሲያ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ጥቃት ፈጸመ። ለጀርመን ለሚቀጥለው ዓመት የ555.4 ቢሊዮን ዩሮ ረቂቅ በጀት ጸደቀ። ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ ከኢራን ጋር ከሥምምነት ላይ ካልደረሰች አገራቸው የጀመረችውን ጦርነት "እንጨርሰዋለን" ሲሉ ዛቱ

DW Amharic-የሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም፤ የዓለም ዜና 05.07.2026

በዛሬው የዓለም ዜና በቀይ ባሕር ትቀዝፍ የነበረች አንዲት ዕቃ ጫኝ መርከብ በየመን ሁዴይዳ የባሕር ክልል አካባቢ ጥቃት ተፈፀመባት መባሉን፣ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ በሂዝቦላህ ላይ የምታካሂደውን ዘመቻ አጠናክራ እንደምትቀጥል መግለጿን፣በእስራኤል እስር ቤት ውስጥ የሚገኙት የጋዛ ሆስፒታል ዳይሬክተር ህይወታቸው አደጋ ላይ ወድቋል መባሉን፣ ሁለተኛ ቀኑን በያዘው የአያቶላህ አሊ ካማኔይ የሀዘን ሥነ ሥርዓት ላይ ልጆቻቸው እና ከፍተኛ የኢራን ባለስልጣናት መገኘታቸውን እንዲሁም ትራምፕ በአሜሪካ 250ኛ ዓመት የነፃነት በዓል ባደረጉት ንግግር የሀገር ፍቅርን ከፓርቲ ፖለቲካ ጋር ቀላቅለዋል በሚል መተቸታቸውን አካቷል።

የሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም፤ የዓለም ዜና 04.07.2026

በዛሬው የዓለም ዜና ፤ የትግራይ ክልል አሁን ያለበት ሁኔታ አሳስቦኛል ሲል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን መግለፁን፣የአውሮፓ እና የአሜሪካ መሪዎች ስደተኞችን ለመጠበቅ እና ለማዋሃድ የበለጠ እንዲሰሩ የሮማ ካቶሊክ ሊቀ ጳጳሥ ማሳሰባቸውን፣ኢራን ለሟቹ መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አሊካሜኒ ብሄራዊ የሽኝት ሥነ ስርዓት ዛሬ በይፋ መጀመሯን፣ጀርመን፤ ቤጂንግ የሩሲያ ወታደሮችን ማሰልጠኗን የሚያሳዩ ዘገባዎች መውጣታቸውን ተከትሎ ቻይናን ማስጠንቀቋን፣አማራጭ ለጀርመን የተባለው መጤ ጠል ፓርቲ ዛሬ መሪዎቹን መምረጡን እንዲሁም ዶናልድ ትራምፕ ለ11 ተከሳሾች ይቅርታ ማድረጋቸውን የሚያስቃኙ ዜናዎች ተካተዋል።

የሰኔ 26 ቀን 2018 የዓለም ዜና 03.07.2026

-በደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ዘይሴ ወረዳ የመንግሥት ታጣቂዎች በከፈቱት ጥቃት 10 ሰዎች መገደላቸዉን የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) አስታወቀ።---የቀድሞዉ የኢራን ላዕላይ መሪ አ,ያቶላሕ ዓሊ ኻምኔይ አስከሬን የሽኝት ሥርዓት ዛሬ ቴሕራን ዉስጥ ተጀመረ።ዩናይትድ ስቴትስና እስራኤል ኢራን ላይ ጦርነት በከፈቱበት ዕለት ባለፈዉ የካቲት ማብቂያ የተገደሉት ኻምኔይ ኢራንን ለ37 ዓመት መርተዋል።86 ዓመታቸዉ ነበር።--ሐሙስ ይቀበራሉ።-የጀርመን የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዩሊያን ናግልስ ማን በከፍተኛ ግፊት ሥልጣኑን ለቀቀ።

የሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና 02.07.2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ኮሬ ዞን ተማሪዎች እስካሁን የዓመቱን የማጠቃለያ ፈተና እንዳልተፈተኑ ወላጆች ገለጹ። መምህራኑ «መንግሥት የኑሮ ውድነትን ለመደጎም ያደረገው ውዝፍ የደመወዝ ጭማሪ በተሟላ ሁኔታ አልተከፈለንም» በሚል ወደ ትምህርት ቤት አልሄዱም ተብሏል። በሰሜናዊ ናይጀሪያ ማለቂያ ባጣው ግጭት ምክንያት ታይቶ የማይታወቅ ረሀብ መከሰቱን ዛሬ የተመድ አስታወቀ። የኬንያ ፍርድ ቤት በስምንት ተማሪዎች ላይ የግድያ ክስ መሰረተ። ዛሬ ማለዳ ሩሲያ በዩክሬን ዋና ከተማ ኪየቭ ላይ ባደረሰችው ጥቃት ቢያንስ 21 ሰዎች መገደላቸውን የከተማዋ ከንቲባ አመለከቱ። 86 ሰዎችም ተጎድተዋል።

የሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና 01.07.2026

የሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም. አርእስተ ዜና አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ የሱዳኑን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል በምህጻሩ RSFን በሰብዓዊነት ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎችና በዘር ማጥፋት ወንጀል ከሰሰ ። ትውልደ-ኢትዮጵያዊቷ ሶሻል ዴሞክራት ሜላት ኪሮስ ትናንት ማክሰኞ በአሜሪካ በዴንቨር አካባቢ የተካሄደውን ምርጫ አሸነፉ። ሜላት ኪሮስ ለ15 ጊዜ የአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑትን ዲያና ደጌትን ነew ያሸነፉት ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን በቀጠር ዋና ከተማ ዶሀ ዛሬ ቀጥተኛ ያልሆነ ንግግር መጀመራቸው ተሰምቷል ።

የሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና 30.06.2026

የተመድ የኢቦላ ወረርሽኝ አፍሪቃን እስከ 3,6 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ያስወጣታል አለ። የኬንያ ፖሊስ በዛሬው ዕለት እገታን በመቃወም አደባባይ የወጡ ናቸው በተባሉ ሰዎች ላይ ጥይት ተኩሶ አንድ ሰው መግለደሉን እማኞች አመለከቱ። ሁለት ሰዎችም በጥይት ተጎድተዋል። የተመድ የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት በሱዳን አል ኦቢድ ጉዳይ አስቸኳይ ክርክር ሊያካሂድ መሆኑ ተገለጸ። በተጠቀሰችው ከተማ ዙሪያ የፈጥኖ ደራሹና ደጋፊዎቹ ኃይሎች መከማቸታቸው ስጋት አስከትሏል። ኢራን ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በመጪዎቹ ቀናት የመገናኘት እቅድ የለኝም አለች። ሁለት የአሜሪካ ልዑካን በኢራን ጉዳይ ለመነጋገር ዛሬ ቀጠር መግባታቸው ተዘግቧል።

DW Amharic የሰኔ 22 ቀን 2018 የዓለም ዜና 29.06.2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የሶማሊያ ፕሬዝደንት ሐሰን ሼክ ማሕሙድ ተገናኙ። ለ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና የሚቀመጡ ተማሪዎች ሞባይል ስልክ፣ ቅንጡ የእጅ ሰዓቶችና ማዳመጫዎች ወደ መፈተኛ ክፍል ይዘው መግባት ተከለከሉ። ኢትዮጵያ አንድ ቢሊዮን ዶላር የተበደረችበት ቦንድ ባለቤቶችን ከሚወክል ጊዜያዊ ኮሚቴ ጋር የዕዳ አከፋፈል ሽግሽግ ለማድረግ በመርኅ ደረጃ ከሥምምነት መደረሱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ። የኬንያ መንግሥት ከአሜሪካ ጋር ሊፈራረም ነው የተባለው የውድ ማዕድናት ፍለጋ “ግልጽነት ይጎድለዋል” የሚል ክስ በፍርድ ቤት ቀረበበት። በጀርመን ኒደር ዛክሰን ግዛት ሽታደ ከተማ በተከፈተ ተኩስ 5 ሰዎች ተገደሉ

የዕሁድ ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ. ም ፤ የዓለም ዜና 28.06.2026

የዛሬው የዓለም ዜና በሳውዲ አረቢያ እና በፈረንሳይ በደረሰ የሄሊኮፕተር እና የአውሮፕላን አደጋ 25 ሰዎች መሞታቸውን፣ በአውሮጳ በተከሰተው ከፍተኛ የሙቀት ማዕበል በአንድ ሳምንት ብቻ ከ1,300 በላይ ሞት መመዝገቡን፣ ቢያንስ 191 ሚሊዮን ሰዎች ለ35 ዲግሪ ሴልሺየስ ሙቀት ይጋለጣሉ መባሉን፣ ኢራን የአሜሪካን ጥቃት ተከትሎ በባህሬን እና ኩዌት ላይ ጥቃት ማድረሷን እንዲሁም የዩክሬንን ጥቃት ተከትሎ የሩሲያው መሪ የሀገራቸውን ደህንነት ለማረጋገጥ ቃል መግባታቸውን አካቷል።

የሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና 27.06.2026

• በኢትዮጵያ የሚገኘው የአውሮጳ ኅብረት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) እያካሔደ ነው የተባለው አስገዳጅ ወታደራዊ ምልመላ የፕሪቶሪያ ግጭት የማቆም ስምምነት በግልጽ የጣሰ ነው ሲል ነቀፈ። • በሱዳን ኤል-ኦቤይድ ከተማ የሚካሄደው ውጊያ ወደ ከፋ ደረጃ ላይ ሊደርስ ይችላል ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስጠነቀቀ። • የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መንግሥት በጎረቤት ሩዋንዳ ላይ በዓለም አቀፉ የወንጀል መዳኛ ፍርድ ቤት (ICJ) ክስ መሰረተች። • ኢራን አሜሪካን "ጦርነቱን ለማቆም የተደረገውን ስምምነት ጥሳለች" ስትል ከሰሰች።

የዓርብ ሰኔ 19 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና 26.06.2026

መቐለ፥ ሕወሓት ለሒውማን ራይትስ ዎች ምላሽ ሰጠ፤ ካርቱም፥ በሱዳን ኤል ኦቤይድ ከተማ ላይ ሌላ ፍጅት እንዳይከሰት አሥግቷል፤ ቱኒስ፥ ኃዋቂዋ ቱኒዚያዊት የ75 ዓመት የመብት ተሟጋች 25 ዓመት እስር ተፈረደባቸው፤ ዋሽንግተን፥ የዩናይትድ ስቴትስ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሔይቲ እና ሶሪያ ዜጎች በገፍ ከአገር እንዲባረሩ የሚያስችል መንገድ ጠረገ፤ ፓሪስ፥ አውሮጳን የመታው የሙቀት ማእበል እንደበረታ ነው፤ ካራካስ፥ ከብርቱው ርእደ መሬት የተረፉትን ለማዳን ርብርቡ ቀጥሏል፤ ኒው ጄርዚ፥ የዓለም ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ እየተገባደደ ነው

የሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና 25.06.2026

የኬንያ ፖሊስ በዛሬው ዕለት ናይሮቢ በሚገኘው ዋና የፖሊስ ጣቢያ አቅራቢያ የተሰበሰቡ ሰልፈኞችን በአስለቃሽ ጭስ በተነ። ቬንዝዌላን ባናወጠው የመሬት መንቀጥቀጥ ቢያንስ የ164 ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን 971 ሰዎች መጎዳታቸውን የሀገሪቱ ጊዜያዊ ፕሬዝደንት አስታወቁ። በርካታ ሃገራት ለእርዳታ እጃቸውን ዘርግተዋል። የኢራን አብዮታዊ ዘብ አዛዥ እስራኤል ከመላ ሊባኖስ መውጣት እንደሚኖርባት አመለከቱ። እስራኤል ሂዝቦላህ ትጥቁን ሳይፈታ ኃይሌን አላወጣም ብላለች። ፈረንሳይ ከሩሲያ ጋር ግንኙነት ያለው ነዳጅ ጫኝ መርከብን በሲሲሊ የባሕር ዳርቻ ላይ መያዟን አስታወቀች። ሩሲያ ድርጊቱን አውግዛ የባሕር ላይ ውንብድና ብላዋለች።

የሰኔ 17 ቀን 2018 የዓለም ዜና 24.06.2026

-ራሱን የሊቢያ «የመረጋጋት መንግሥት» ብሎ የሚጠራዉ የምሥራቅ ሊቢያ ስብስብ የኢትዮጵያ፣ የሶማሊያ፣ የኤርትራና የሱዳን ዜጎች ሊቢያ እንዳይገቡ አገደ።---አዉሮጳን የገለበዉ የሙቀት ማዕበል የሰዎች ሕይወት እያጠፋ፣የትምሕርት ሒደት፣ሥራና እንቅስቃሴንም እያስተጓጎለ ነዉ።አለቅጥ የናረዉ ሙቀት ያንገበገባቸዉ አንዳድ ሰዎች ዘለዉ ወንዝ፣ኩሬና ገንዳ ዉስጥ እየገቡ ሞተዋል።--የዓለም የአዉቶሚክ ተቆጣጣሪ ድርጅት (IAEA) የኢራንን የኑክሌር ተቋማትና ንጥረ ነገር በቅርቡ እንደሚፈትሽ አስታወቀ።ኢራን ግን የኑክሌር ጉዳይ የሚነሳዉ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ያደረገችዉ ሥምምነት ገቢራዊነት ሲረጋገጥ ብቻ ነዉ ትላለች።

የሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ ም የዓለም ዜና 23.06.2026

ግብፅ ከህገ-ወጥ የወርቅ ማዕድን ጋር በተያያዘ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በቁጥጥር ስር አዋለች።ዩጋንዳ ውስጥ አንድ አዲስ ሰው ላይ ኤቦላ ተረጋገጠ፤ በጠቅላላው 20 ሰዎች ተይዘዋል እስራኤል ወደፊት የጦር መሣሪያ አቅርቦትን በተመለከተ የዩናይትድ ስቴትስ ጥገኛ መሆን እንደማትፈልግ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ አስታወቁ። አምስት ልዑካንን ያቀፈ የታሊባን ቡድን ዛሬ ከአውሮጳ ህብረት ኮሚሽን ተወካዮች ጋር ለመምከር ብራስልስ ገባ። ዶይቸ ቬለ DW በየዓመቱ የሚያካሂደው ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙኃን መድረክ ዛሬ ማክሰኞ በቦን ከተማ መካሄድ ጀመረ።

የሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና 22.06.2026

የኬንያ የሰራተኛ ጉዳይ ሚኒስትር፤ ወጣቶችን ለሩስያ በወታደርነት በመመልመል እንደሚጠረጠሩ ተገለጸ። በቀጠር በአንድ የተፈጥሮ ጋዝ ማምረቻ በደረሰ ፍንዳታ 13 ሰዎች ሲሞቱ በ 54 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የቀጠር የሐገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። በዮናይትድ ስቴትስና ኢራን መካከል በስዊዘርላንድ ሲካሄድ የነበረ ንግግር በጥሩ መንፈስ መጠናቀቁን የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር አስታወቁ።የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር ከጠቅላይ ሚኒስትርነት ስልጣናቸውንና ከሌበር ፓርቲ መሪነታቸው በገዛ ፈቃዳቸው እንደሚለቁ አስታወቁ።

የሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና 21.06.2026

የዛሬው የዓለም ዜና በአብዛኛዎቹ አካባቢዎች ገዡ ፓርቲ ብልፅግና 90 በመቶ ድምፅ ማግኘቱን ምርጫ ቦርድ መግለጹን፣በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ነፃ እና ገለልተኛ ተቋም ሆኖ መስራቱን የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ መናገራቸውን፣በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሴቶች ያለስጋት እንዲሳተፉ ሁሉን አቀፍ ርምጃ ተወስዷል ሲል የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር ማለቱን እና በምርጫ ወቅት ጥቃቶች መፈፀማቸውን መጠቆሙን እንዲሁም ገዥው ፓርቲ ብልፅግና በቀጣይ አምስት የስልጣን አመታት የነበሩ ችግሮችን እንዲቀርፍ ነዋሪዎች መጠየቃቸውን አካቷል። # ምርጫ2018 #EthiopiaElection2026

የሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና 20.06.2026

• የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኤርትራ ጉዳይ ልዩ መርማሪ በሀገሪቱ የሰብአዊ መብት ጥሰት እየተባባሰ መምጣቱን አስታወቁ። • በእስር ላይ የነበረችው ጋዜጠኛ ሳልሳዊት ባይነሳኝ መፈታቷን ቤተሰቦቿ ለዶቼ ተናገሩ። • በምስራቃዊ ሊቢያ የባህር ዳርቻ የአንድ ህጻን ሴት ልጅን ጨምሮ በትንሹ የ15 ፍልሰተኞች አስከሬን ተገኘ። • አፍሪካ እና የካሪቢያን ሀገራት መሪዎች ጥቁሮችን ለባርነት የዳረጉ ያሏቸውን ሃገራት ካሳ እንዲከፍሉ ጠየቁ ። • ኢራን የሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥን በድጋሚ ዘጋች። • አውሮጳን እያናወጠ የሚገኘው አስከፊ የሙቀት ማዕበል በጀርመን ፣ፈረንሳይ እና ጣልያን ብርቱ ተጽዕኖ ማሳደሩ ተነገረ።

የሰኔ 12፣ ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና 19.06.2026

• በትግራይ ክልል ለወታደራዊ ስልጠና የሚደረገው የአፈሳ ዘመቻ ብርቱ ትችት እና ተቃዉሞ መቀስቀሱ ተዘገበ ። • በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት ዛሬ ዓርብ አስጠነቀቀ። • እስራኤል እና የሊባኖሱ ታጣቂ ቡድን ሄዝቦላህ ቀደም ሲል አድርገው የነበረውን የተኩስ አቁም ስምምነት ለማደስ መስማማታቸው ተገለጸ። • የአውሮጳ ኅብረት መሪዎች በሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት ዙሪያ የኅብረቱን ጥቅሞች ለማስከበር ከሩስያ ጋር ቀጥተኛ ያልሆነ ግንኙነት ለመጀመር ያቀረቡት ሐሳብ ሳይሳካ ቀረ።

የሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና 18.06.2026

አርዕስተ ዜና -ዩናይትድ ስቴትስ «አክራሪ» ባለቻቸዉ የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አባላትና በቤተሰቦቻቸዉ ላይ ያነጣጠረ የቪዛ እገዳ ጣለች። ዩናይትድ ስቴትስ የቪዛ እገዳዉን የጣለችዉ / በትግራይ ክልል ሠላም ለማስፈን የተደረገዉን ስምምነት በሚጥሱና ከሚጥሱ ወገኖች ጋር በሚተባበሩ ሰዎች ላይመሆኑን አስታውቃለች። -የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባለፈዉ ግንቦት በተደረገዉ ምርጫ ሒደት ቅሬታ ከቀረበባቸዉ 128 የምርጫ ክልሎች ለ85ቱ ዉሳኔ መስጠቱን ዐሳወቀ። -በኤልኒኞ ምክንያት ኢትዮጵያውያን ጨምሮ 22 ሀገራት ለከፍተኛ አደጋ መጋለጣቸውን FAO እና የWFP ዛሬ በጋራ አሰሳቡ።

የሰኔ 10 ቀን 2018 የዓለም ዜና 17.06.2026

-የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ያስገነባችዉ ግድብ ግብፅን ለብዙ ችግሮች አጋልጧል አሉ።ትራምፕ የግብፅ አቻቸዉን ዛሬ ሲያነጋግሩ እንዳሉት መስተዳድራቸዉ ሁለቱን ሐገራት ለማግባባት እንደሚጥር አስታዉቀዋልም።---በ13 ሐገራት ወይም ግዛቶች የሚኖር በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ሕዝብ አስቸኳይ ርዳታ ካላገኘ ለአስከፊ ረሐብ እንደሚጋለጥ የተባበሩት መንግሥታት ሁለት ድርጅቶች አስታወቁ።ድርጅቶቹ እንደሚሉት ሱዳን፣ ሶማሊያና ጋዛን ጨምሮ ለችግር የተጋለጡ 266 ሚሊዮን ሰዎች በቂ ርዳታ አያገኙም።---የቡድን 7 አባል ሐገራት መሪዎች በማደግ ላይ ባሉ ሐገራት ላይ ያለዉን ዕዳ ለማቃለል ቃል ገቡ።

የሰኔ 9 ቀን 2018 የዓለም ዜና 16.06.2026

በዚምባብዌ አንድ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ከባቡር ጋር በመላተሙ ቢያንስ 9 ሰዎች ሲሞቱ 25 መቁሰላቸውን የሐገሪቱ የሐገሪቱ ባለስልጣናት አሳወቁ። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሐገራቸው ከአሜሪካ ጋር የመጨረሻው የሰላም ስምምነት በመጨው አርብ በስዊትዘርላንድ እንደሚፈረም አረጋገጡ።ዩክሬን በሞስኮ አቅራቢያ የሚገኘውን የሩስያ የነዳጅ ማጣሪያ ማጋየቷ ተሰማ። ጀርመን ወደ 30 የሚሆኑ የአፍጋኒስታን ዜጎች ከሐገር ማባረሯን አሳወቀች።

Listen to the የዓለም ዜና podcast in Replaio

Radio and podcasts in one app - free, with no sign-up. Install today and do not miss the launch

Get it on Google Play

Replaio is not a podcast publisher; show names, artwork and audio belong to their authors and are distributed through public RSS feeds.