DW
በሳይንስ እና ቴክኒክ ላይ ያተኩራል። | Deutsche Welle
ሳይንሳዊ እና ስነ ቴክኒካዊ ጉዳዮችን እና ለህብረተሰቡ ያላቸቸውን ጠቀሜታ ይመለከታል።
Author
DW
Category
Podcast website
Latest episode
Jul 8, 2026
Where to listen?
Podcasts in the app Replaio Radio Coming soonPodcasts are coming to the app soon. Install now and be the first to see a whole new take on podcasts
Episodes
የሰውሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ በህግ እንዲመራ ጥሪ ቀረበ 08.07.2026 10:15
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለመጀመሪያ ጊዜ የሰውሰራሽ አስተውሎት AI አስተዳደርን የሚመለከት ዓለም አቀፍ ውይይት በዚህ ሳምንት አካሂዷል።በዚህ ውይይት ፤የሰውሰራሽ አስተውሎት በተለይም በልጆ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን አሉታዊ ተጽዕኖ ለማስቀረት በህግ መመራት እንዳለበት ጥሪ ቀርቧል። ቴክኖሎጂውን ለጦርነት መጠቀም አሳሳቢ ነው ተብሏል።
እንደ ቲክቶክ ያሉ ዲጅታል መድረኮች ለስዓትት እዚያው እንድንቆይ ለምን ያደርጋሉ? 01.07.2026 10:51
ቴክኖሎጂ ኩባንያዎች እንደ የቲክቶክ ያሉ የአጫጭር ቪዲዮ መድረኮች የተነደፉት ሱስ እንዲያስይዙ ሆነው ነው በሚል የሚቀርብባቸውን ክስ ሲያስተባብሉ ቆይተዋል። በቅርቡ የወጣ አንድ ጥናት እንዳረጋጠው ግን የአጫጭር የቪዲዮመድረኮች የተነደፉት ተጠቃሚዎችን የበለጠ ተሳታፊ እንዲሆኑ በሚያደርጉ የሰዎች የሥነ-ልቦና እና የነርቭ ስርዓቶች ላይ ተመስርቶ ነው።
ስልክ እና አድራሻን በቀላሉ ለማግኘት የሚያግዘው ዲጅታል መድረክ 24.06.2026 9:51
ኢትዮጵያ ውስጥ ስልክ እና አድራሻ ማግኘት ተቸግረዋል? ብሩክ ጌታቸው እና ብሩክ እንድሪያስ በተባሉ ሁለት ወጣቶች የተሰራው ዲጅታል መድረክ ችግሩን የሚፈታ ይመስላል። ዲጅታል መድረኩ በኢትዮጵያ የሚገኙ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት፣የአደጋ ጊዜ ቁጥሮችን እና አድራሻዎችን በቀላሉ ተደራሽ የሚያደርግ መሆኑተገልጿል።
ክፉ መካሪው ቻት ጂፒቲ 17.06.2026 12:49
እንደ ቻት ጂፒቲ ያሉ ዲጂታል መድረኮች ከቀላል እስከ ውስብስብ ሀሳቦች ድረስ መረጃ በመስጠት ነባሩን የጉግል ፍለጋ በመተካት ላይ ይገኛሉ።ያም ሆኖ ቻት ጂፒቲን የመሳሰሉ በሰው ሠራሽ አስተውሎት የተመሰረቱ ዲጅታል መድረኮች ልጆችን ለአደጋ በማጋለጥ ፣ሱስ በማስያዝ፣ እና ተጠቃሚዎቹ ራሳቸውን እንዲያጠፉ በመገፋፋት በተደጋጋሚ ይከሰሳሉ።
ድምፅ እና ምስል የሚቀርፁት የዓይን መነፅሮች 27.05.2026 11:17
እነዚህ የስማርት መነፅሮች ካሜራ፣ ማይክሮፎን፣ ድምጽ ማጉያዎች፣ ዳሳሾች/ሴንሰሮች/ እና እንደ ኮምፒውተር ቺፕስ ያሉ ትናንሽ የኤሌክትሮኒክስ ክፍሎች ያሏቸው ሲሆን፤ ከኢንተርኔት ጋር በብሉቱዝ ወይም በዋይፋይ ይገናኛሉ።በዚህም ያለ እጅ ንክኪ በድምፅ ትዕዛዝ ብቻ ሙዚቃ ማዳመጥ፣ የስልክ ጥሪ መቀበል፣ ቢዲዮ መቅረፅ እና ፎቶ ማንስሳትም ይችላሉ።
ምርጫ እና ዲጂታል ቴክኖሎጂ 20.05.2026 11:47
ዲጅታል ቴክኖሎጂ በአሁኑ ወቅት በእያንዳንዱ የዕለት ተዕለት ህይወታችን ውስጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወተውን ያህል፤ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓቶችን ለመገንባት በሚካሄዱ ምርጫዎች ውስጥም አንድ አካል እየሆነ መጥቷል። ከመራጮች ምዝገባ እስከ የድምጽ ቆጠራ እና የውጤት ማሳወቂያ ድረስ ቴክኖሎጂ ምርጫዎች የሚካሄዱበትን መንገድ እየቀረጸ ይገኛል።
የ115 ሀገራት ባለሙያዎች በተሳተፉበት ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ውድድር ያሸነፈው ኢትዮጵያዊ ወጣት 13.05.2026 10:46
ናትናኤል ጌጤነው የተባለ 24 ዓመት ወጣት ሰሞኑን አማዞን ባዘጋጀው ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ውድድር አሸናፊ ሆኗል። ወጣቱ አሸናፊ የሆነው አይቪ የተባለ ለትምህርት አጋዥ የሆነና ያለኢንተርኔት የሚሰራ የሰውሰራሽ አስተውሎት ዲጅታል መድረክ በመፍጠር ነው። ወጣቱ ለወደፊቱም ኢትዮጵያን የሰውሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ማዕከል የማድረግ ህልም አለው።
የሳይበር ጉልበተኞች ጥቃት በወጣት ተፅዕኖ ፈጣሪ ሴቶች ላይ 06.05.2026 12:15
የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ሰዎች ተሰጦዎቻቸውን እንዲያወጡ፣ ሀሳቦችን እንዲያካፍሉ እና መስተጋብር እንዲፈጥሩ ያግዛሉ። በዚያው ልክ፤መድረኮችቹ የሳይበር ጉልበተኞች ጥቃት የሚስፋፋባቸው ቦታዎች እየሆኑ ነው። በተለይ ወጣት ሴቶች ለዚህ ጥቃት የበለጠ ተጋላጭ ሲሆኑ፤ራስን እስከማጥፋት የሚያደርስ ሥነልቡናዊ ጫና እንደሚፈጥርም ጥናቶች ያሳያሉ።
የናሳ አዳዲስ ፕላኔቶች ፍለጋ 29.04.2026 10:42
ናሳ ያለፈው ማክሰኞ፣ በጎርጎሪያኑ ሚያዚያ 22 ቀን ፣ ከስርዓተ ፀሐይ/ Solar System/ ውጭ ያሉ ፕላኔቶችን ለመፈለግ እና ያልታወቀ ቁስ ሀይልን ሚስጥሮችን ለመመርመር አዲስ ቴሌስኮፕ ይፋ አድርጓል። በመጭው መስከረም ተልዕኮውን ለመጀመር ወደ አፅናፈ ዓለም ወይም ዩንቨርስ የምትጓዘው ይህቺ ቴሌስኮፕ ሮማን የሚል ስም ተሰጥቷታል።
የሮቦት አትሌቶች በማራቶን ውድድር አሸናፊ ሆኑ 22.04.2026 9:04
ሰሞኑን በቻይና ቤጂንግ በተካሄደ ግማሽ ማራቶንን ውድድር ሮቦቶች ከሰዎች ጋር የሩጫ ውድድር አድርገዋል።በውድድሩ ጀርመን፣ ፈረንሳይ እና ብራዚልን ጨምሮ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ከ100 በላይ ሮቦቶች ተሳትፈዋል።አሸናፊው፣ ላይትኒግ የተባለ የቻይና ሮቦት ሲሆን፤ የ21 ኪሎ ሜትር ውድድሩን በ50 ደቂቃ ከ26 ሰከንድ ውስጥ አጠናቋል።
ቲክ ቶክ፣ ፌስቡክ እና ዩቱዩብ ሱስ የሚሆኑት ለምንድነው? 01.04.2026 4:23
እንደ ፌስቡክ፣ ዩቲዩብ እና ቲኮክ ያሉ ዲጅታል መድረኮች ለተግባቦት ብቻ የሚያገለግሉ ዲጅታል መድረኮች ብቻ አይደሉም። ባለሙያዎች እንደሚሉት እነዚህ ዲጅታል መድረኮች ትኩረታችንን ለመሳብ እና ይዞ ለማቆየት ጭምር በጥንቃቄ የተነደፉ ናቸው።ለተጠቃሚዎቹ መረጃ የሚጠቁሙበት እና ለፍላጎት የሚስማሙ ይዘቶችን የሚያቀርቡበት መንገድም በዚህ የተቃኘ ነው።
ጥላቻ እና ሀሰተኛ መረጃን ያስፋፉት በኤአይ የሚሰሩ ይዘቶች 25.03.2026 12:06
የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ማሽን ሰወችን ተክቶ እንዲሰራ በማድረግ ጊዜን ፣ገንዘብን እና የሰው ሀይልን ይቆጥባል።ጥራትን እና ምርታማነትን በመጨመር ረገድም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል። ያም ሆኖ ቴክኖሎጂው ሀሰተኛ ድምፅን፣ ምስልን እና ቪዲዮዎችን አስመስሎ በመስራት ሀሰተኛ ወይም የተዛባ መረጃ በማሰራጨት ረገድም አሉታዊ ጎን አለው።
የሰው ሠራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ፣በትምህርት እና ጤና 18.03.2026 9:32
የሰው ሠራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ፣በዓለም ላይ ከዐይን ጥቅሻ በፈጠነ ሁኔታ እያደገ ይገኛል። ይህንን በፍጥነት እያደገ ያለ ቴክኖሎጂ ኢትዮጵያ ውስጥ በጤና እና ትምህርት ዘርፍ ጥቅም ላይ ለማዋል እና የስልጠና ድጋፍ መሆኑን ፒፕል ቱ ቲፕል የተባለው ተቋም ገልጿል።ተቋሙ በኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን አሜሪካ ውስጥ የተቋቋመ ነው።
የሰው ሠራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ፣በትምህርት እና ጤና 18.03.2026 9:32
የሰው ሠራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ፣በዓለም ላይ ከዐይን ጥቅሻ በፈጠነ ሁኔታ እያደገ ይገኛል። ይህንን በፍጥነት እያደገ ያለ ቴክኖሎጂ ኢትዮጵያ ውስጥ በጤና እና ትምህርት ዘርፍ ጥቅም ላይ ለማዋል እና የስልጠና ድጋፍ መሆኑን ፒፕል ቱ ቲፕል የተባለው ተቋም ገልጿል።ተቋሙ በኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን አሜሪካ ውስጥ የተቋቋመ ነው።
በታዋቂ ሴቶች ላይ የበረታው ዲጅታል ጥቃት በኢትዮጵያ 11.03.2026 13:33
አዲስ ፓወር ሃውስ የተባለ ሀገር በቀል ተቋም በቅርቡ ባወጣው ጥናት፤ በኢትዮጵያ ታዋቂ ሴቶችን ኢላማ ያደረገ ዲጅታል ጥቃት ጨምሯል።ጥናቱ በቲክቶክ፣በፌስቡክ፣በቴሌግራም፣በዩቱብ እና በሊንክዴን ላይ በተለጠፉ1307 ይዘቶች ላይ ትንተና ያደረገ ሲሆን፤ በዚህም በታዋቂ ሴቶች ላይ ጥቃቱ የበረታ መሆኑን የተቋሙ ዳይሬክተር ሀና ለማ ገልፃለች።
Similar podcasts
Replaio is not a podcast publisher; show names, artwork and audio belong to their authors and are distributed through public RSS feeds.