ECFC in Finland

Ethiopian Christian Fellowship Church in Finland

Religion EN ↓ 447 episodes

This is a podcast from the Ethiopian Christian Fellowship in Finland, where you can listen to biblical teachings, messages, and sermons. May God bless all our listeners.

Author

ECFC in Finland

Category

Religion

Podcast website

ecfc-finland.org

Latest episode

Jul 5, 2026

Where to listen?

Podcasts in the app Replaio Radio Coming soon

Podcasts are coming to the app soon. Install now and be the first to see a whole new take on podcasts

Get it on Google Play Install for free Android 5M+ downloads · 4.8 rating iOS soon

Episodes

097_የኢየሱስ ሞት ምን አመጣልን? ክፍል 1 12.04.2020

በፋሲካ ልዩ ፕሮግራም ላይ በወንድም ያቬሎ ናታዬ የቀረበ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት ክፍል 1::

096_ኢየሱስ ለምን ራሱን የሰው ልጅ አለ? 12.04.2020

በፋሲካ ፕሮግራም ላይ በወንድም ተከለ ማርቆስ (ዶ/ር) የቀረበ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት::

095_የእግዚአብሔር ማስጠንቀቂያ ክፍል 2 05.04.2020

"የእግዚአብሔር ማስጠንቀቂያ" በሚል ርዕስ በወንጌላዊ ዘገዬ መኮንን የቀረበ የእግዚአብሔር መልዕክት ሁለተኛው ክፍል::

094_የእግዚአብሔር ማስጠንቀቂያ! 29.03.2020

የእግዚአብሔር ማስጠንቀቂያ በሚል ርዕስ በወንጌላዊ ዘገዬ መኮንን የቀረበ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት::

093_ለጥሪው ምላሽ የምንሰጠው እንዴት ነው? 22.03.2020

"ለጥሪው ምላሽ የምንሰጠው እንዴት ነው?" በሚል ርዕስ በወንድም ያቬሎ ናታዬ የቀረበ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት:: ለጥሪው ምላሽ የምንሰጠው እንዴት ነው? 1) ጥሪውን በመለየትና ጠሪውን በመከተል 2) ራስን በመካድና የራስን መስቀል በመሸከም 3) የነፍሳችንን ዋጋ በማወቅና ነፍሳችንን በማዳን ይሁን! የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች: ማር. 8:34-38/ ማቴ. 9:9/ ማር. 2:14/ ማር. 10:17-22/ 1ቆሮ. 1:26/ ኤፌ. 4:1-3/ ሮሜ 8:14/ 1ዮሐ. 2:15-16/ ሉቃ. 9:23/ ገላ. 5:16-18/ ሉቃ. 12:19-21

092_ምን አደርግልህ ዘንድ ትወዳለህ? 08.03.2020

"ምን አደርግልህ ዘንድ ትወዳለህ?" በሚል ር ዕስ በወንጌላዊ ዘገየ መኮንን የቀረበ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት:: የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች: 1ነገ. 3:1-15/ዮሐ. 5:1-9/1ጢሞ. 2:1-4

091_መንፈሳዊ ነገሮችን ማወቅ! 01.03.2020

"መንፈሳዊ ነገሮችን ማወቅ" በሚል መሪ አሳብ በወንጌላዊ ዘገየ መኮንን የቀረበ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት:: ይህ ክፍል "እግዚአብሔርን ማወቅ" በሚል ርዕስ በተከታታይነት የቀረበው ትምህርት ክፍል ነው:: የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች: 1ቆሮ. 12:1-7/ገላ. 5:22/1ቆሮ. 1:7/1ቆሮ. 14:12,26/1ቆሮ. 14:1, 39-40/ምሳሌ 15:22/ምሳሌ 19:21

090_እግዚአብሄርን ማወቅ ክፍል 3 (በወንጌላዊ ዘገዬ መኮንን) 23.02.2020

090_እግዚአብሄርን ማወቅ ክፍል 3  (በወንጌላዊ ዘገዬ መኮንን) ወዳጆች ሆይ፥ፍቅር ከእግዚአብሔር ስለ ሆነ፥ የሚወደውም ሁሉ ከእግዚአብሔር ስለ ተወለደ እግዚአብሔርንም ስለሚያውቅ፥ እርስ በርሳችን እንዋደድ።  ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም፥ እግዚአብሔር ፍቅር ነውና። 1ኛ ዮሐ 4:7 እና  ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም በሚለው ቃል  በመመልከት ከ1ኛ ቆሮ13:1-7 ባለው ላይ ቃል ላይ ተመስርተን ራሳችንን እናይ ዘንድ የሚያግዝ መልእክት ነው::

089_ወንጌልን እንዴት እናገልግል? 16.02.2020

"ወንጌልን እንዴት እናገልግል?" - መልካሙን ሥራ ለመሥራት ተፈጠርን በሚል ርዕስ በወንድም ተከለ ማርቆስ (ዶ/ር) የቀረበ የእግዚአብሔር ቃል ተከታታይ መልዕክት ቀጣይ ክፍል:: የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች: ሮሜ 10:5-14/ኤፌ. 5:14-20/ፊል. 1:15-18/ቲቶ 1:9-11

088_አትለፈኝ! 09.02.2020

"አትለፈኝ" በሚል ርዕስ በእህት ለምለም ጌታቸው የቀረበ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት:: የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች: ማር. 6:45-51/ዘፍ. 18:1-5/መዝ. 27:6-9

087_ወንጌልን በመሥራት መልካሙን ሥራ ማድረግ! 02.02.2020

"ወንጌልን በመሥራት መልካሙን ሥራ ማድረግ" በሚል ርዕስ በወንድም ተከለ ማርቆስ (ዶ/ር) የቀረበ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት:: የወንጌልን ሥራ ለመሥራት የሚያስፈልጉ ነገሮች: 1) ጸሎት: ማቴ. 9:35-38 2) ልባምና የዋህ መሆን: ማቴ. 10:17 3) ፍርሃትን ማስወገድ: ማቴ. 10:24-28 4) መንፈስ ቅዱስን መታመን: ማቴ. 10:19-20/ ዮሐ. 20:21 5) ለመላክ መታዘዝና መሄድ: ማቴ. 10:16/ ማር. 16:15 6) መጽናት: ማቴ. 10:22-23

086_ፍጻሜያችንን እንመልከት! 26.01.2020

"ፍጻሜያችንን እናስብ/እንመልከት!" በሚል ርዕስ በወንጌላዊ ዘገየ መኮንን የቀረበ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት:: የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች: ራዕ. 7:9-17/መክ. 12:13/መክ. 7:3-4/

85_ጨምሩ ክፍል _4 19.01.2020

84_ጨምሩ ክፍል _4 በወንድም ያቬሎ ናታዬ በመንፈሳዊ ህይወት ለመጨመር መለኮታዊ ባህርይን መላበስ በ2ኛ ጴጥሮስ 1:1-11ባለው መልእክት ላይ የተመሰረተ ሀ-የእድገት አለመኖር ውጤት እንደ መንፈሳዊ እውርነት እና የራስን ሃጢአት አለማስተዋል: ለ-የመንፈሳዊ እድገት መኖር ውጤት ስራፈቶች እና ፍሬቢሶች እንዳንሆን ይረዳል:: ሐ-ወደ እ/ር መንግስት መግባት በሙላት እንዲሆንልን ይረዳል::

084_ጨምሩ! ክፍል 3 12.01.2020

"ጨምሩ!" በሚል ርዕስ በ2 ጴጥ. 1 ላይ ተመሥርቶ በወንድም ያቬሎ ናታዬ የቀረበ ተከታታይ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት 3ኛ ክፍል::

083_የሰው ስራ እና የእግዚአብሄር ስራ 05.01.2020

083_የሰው ስራ እና የእግዚአብሄር ስራ በፓስተር ሳምሶን ስምኦን አቤቱ ስራህን ሰርተህልናልና ሰላምን ትሰጠናለህ:: ኢሳ 26:12 ሰዎች የራሳቸውን ስራ የሚሰሩበት ጊዜ አለ እግዚአብሄር ደግሞ የራሱን ስራ የሚሰራበት ጊዜ አለ በዘፍ 15:1 ጀምሮ ባለው ላይ የተመሰረተ ከእግዚአብሄር ቃል መልእክት

082_እግዚአብሔርን ማወቅ ክፍል 2 01.01.2020

"እግዚአብሔርን ማወቅ" በሚል ርዕስ በወንጌላዊ ዘገዬ መኮንን የቀረበ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት ቀጣይና የመጨረሻ ክፍል:: የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች: /ለ) እግዚአብሔርን ማወቅ ራሱ ምንድን ነው? 1) የእግዚአብሔርን ህይወት መካፈል ነው መዝ. 46:10፣ ዮሐ. 4:10፣ ዮሐ. 14:27፣ 2) እግዚአብሔርን መታዘዝ ነው ኤር. 22:16 3) እውነተኛ አንድነት በቅዱሳን ኅብረት ማድረግ ነው ኤፌ. 4:13፣ 4) የህይወት ልምምድ ነው ኢዮ. 42:2-3፣ 2ጢሞ. 1:12 ሐ) እግዚአብሔርን አለመፈለግ የሚያመጣው ፍርድ ሮሜ 1:28፣ ዳን. 4:25 መ) ማጠቃለያ: ሆሴ. 6:3/

081_እግዚአብሔርን ማወቅ ክፍል 1 29.12.2019

"እግዚአብሔርን ማወቅ" በሚል ርዕስ በወንጌላዊ ዘገየ መኮንን የቀረበ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት የመጀመሪያው ክፍል:: የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች: መግቢያ/ኢሳ. 1:3፣ 1ሳሙ. 2:3፣ ፊል. 3:9-11፣ ኤፌ. 1:16-19/ ሀ) እግዚአብሔርን ማወቅ ለምን? የዘላለም ህይወት ነው: ዮሐ. 17:1-3፣ ለእግ/ር ህዝብ ዋና ነገር ስለሆነ: ዘዳ. 8:3፣ ሆሴዕ 6:6፣ እግዚአብሔርን ማወቅ ከስህተት ይጠብቃል: ማቴ. 22:29፣ እግዚአብሔርን ማወቅ የእግዚአብሔርን ቁጣ ያርቃል: ሆሴዕ 4:1፣ ከጥፋት ይከልላል. ሆሴዕ 4:6፣ ለ) እግዚአብሔርን ማወቅ ራሱ ምንድን ነው? ማስተዋልን ማግኘት ነው: ኢሳ. 6:1፣ ራዕ. 4:1፣ ማቴ 16:13-...

080_ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ! 08.12.2019

"ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ" በሚል ርዕስ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደትን አስመልክቶ በወንጌላዊ ዘገዬ መኮንን የቀረበ የእግዚአብሔር መልዕክት:: የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል: /ሉቃ. 1:26-35/

079_ጨምሩ ክፍል 2 01.12.2019

ጨምሩ በሚል ርዕስ በ2 ጴጥ. 1 ላይ ተመሥርቶ በወንድም ያቬሎ ናታዬ የቀረበ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት ቀጣይ ክፍል::

078_ጨምሩ ክፍል 1 24.11.2019

078_ጨምሩ ክፍል 1 በወንድም ያቬሎ ናታዬ በመንፈሳዊ ህይወት ለመጨመር መለኮታዊ ባህርይን መላበስ 2 ጴጥ 1:1-11 ላይ የተመሰረተ 0.መግቢያ መጽሃፉና መልእክቱ 1.እ/ርና የሰው መለኮታዊ ማንነት 2.የተሰጠን የመለኮት ሃይልና ተስፋ ምንድናቸው:: 3.የመለኮቱ ሃይል እጅግ ታላቅና ክቡር የሆነው ተስፋ ለምን ተሰጠን:: 4.የመለኮታዊ ባህርይና የመንፈሳዊ ህይወት መሰረቶች (1ኛ.የሰው ድርሻ እና 2ኛ. የእ/ር ድርሻ)

077_ለምንድነው ዘወትር መጸለይ የሚያስፈልገን? 17.11.2019

077_ለምንድነው ዘወትር መጸለይ የሚያስፈልገን ወንድም ዶ/ር ተከለ ማርቆስ  በእለቱ የቀረበ የእግዚአብሄር ቃል መልእክት:  ሁልጊዜ ጸልዩ የሚለውን ቃል ላይ በመመስረት "ለምንድነው ዘወትር መጸለይ የሚያስፈልገን?" ለሚለው ምላሽ ይሆን ዘንድ በአስር ዋና ዋና ነጥቦች ከፋፍሎ  የሚያስረዳ በትምህርት መልክ የቀረበ መልእክት:: ጥቅሶች በጥቂቱ . ከእ/ር ጋር ህብረት ለማድረግ መዝ 42:1,ጥበብን ለማግኘት ያእ1:5, ከክፋት ለመጠበቅ መዝ20:1,ከፍርሃት እና ከጭንቀት ለመወጣት ፊሊ 4:4, እና... መዝ 32:1,ሉቃ 22:40 ,ሮሜ10:14,ኤፌ 1:15 ሌሎችም

076_ጸሎት 10.11.2019

"ጸሎት የአምልኮ ዋና ክፍል" በሚል አሳብ ላይ ተመሥርቶ በወንድም ተከለ ማርቆስ (ዶ/ር) የቀረበ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት:: መልዕክቱ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ ያስተማረውን ጸሎት መሠረት አድርጎ እኛም እንደ ክርስቶስ ተከታዮች ጸሎታችን ምላሽ ያለው እንዲሆን እንዴት መጸለይ እንደሚገባን ያስረዳል:: የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች: ማቴ. 21:22፣ 6:9-13/ሉቃ. 11:1-5/ዮሐ. 15:7/ያዕ. 4:3/ምሳ. 3:5

075_የወንድሙ ጠባቂ ማን ነው? 03.11.2019

"የወንድሙ ጠባቂ ማን ነው? ቁምና ልብህን ፈትሽ ቅጥርህንም ጠብቅ!" በሚል ርዕስ በእህት ለምለም ጌታቸው የቀረበ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት:: የመልዕክቱ ማዕከላዊ ሐሳብ ልክ እንደ ቃየን የወንድሞቻችንን ክፋት (ሞት) የምንጠብቅ ሳንሆን ልክ እንደ ሙሴ እህት ወንድሞቻችንን ከክፋት (ከሞት) የምንጠብቅ እንድንሆንና በክርስቶስ የተሰጠንን አንድነትና ኅብረት አስበን በዓለም ውስጥ እንዳሉት የጥፋት መሣሪያ ላለመሆን ልባችንን እንድንጠብቅ ማሳሰብ ነው:: የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች: ዘፍ. 4:1-10/1ቆሮ 1:9-10/ዘጸ. 2:1-10/ምሳ. 18:19-21

074_[ለታላቁ ተልዕኮ] ንቁ! 27.10.2019

"ንቁ" በሚል ርዕስ በፓስተር ሰሎሞን አምደ የቀረበ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት:: የመልዕክቱ ማዕከላዊ ሀሳብ ሰዎችን ከዘላለም ጥፋት ለማዳን ወንጌልን መመስከር የእያንዳንዱ አማኝ ደቀ መዝሙር ኃላፊነት መሆኑንና ለወንጌላዊያን ብቻ የሚተው ሥራ አለመሆኑን አጽንዖት ሰጥቶ መግለጽ ነው:: የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች: ማቴ. 28:18-20/ሐዋ. 1:8/ማቴ. 13:24-30

073_በውስጥህ/ሽ ወንዝ አለ! 25.10.2019

ማክሰኞ ምሽት (22.10.2019) "በውስጥህ/ሽ ወንዝ አለ!" በሚል ርዕስ በፓስተር ሰሎሞን አምዴ የቀረበ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት:: የመልዕክቱ ዋና ትኩረት ለኢየሱስ ክርስቶስ ህይወቱን የሰጠና መንፈስ ቅዱስን የተቀበለ ማንኛውም ሰው የሌሎችን ህይወት መለወጥ የሚችል እምቅ መንፈሳዊ አቅም (ወንዝ) በውስጡ እንዳለ በእግዚአብሔር ቃል መሠረት መተንተንና ማስገንዘብ ነው:: የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች: ሕዝ. 47:1-12/ራዕ. 22:1-2/ዮሐ. 7:38

Listen to the Ethiopian Christian Fellowship Church in Finland podcast in Replaio

Radio and podcasts in one app - free, with no sign-up. Install today and do not miss the launch

Get it on Google Play

Replaio is not a podcast publisher; show names, artwork and audio belong to their authors and are distributed through public RSS feeds.