Leoul Zewelde

Sost kilo

Fiction AM ↓ 38 episodi

Stories.https://linktr.ee/sostkilo

Autore

Leoul Zewelde

Categoria

Fiction

Sito del podcast

t.me

Ultimo episodio

20 ago 2023

Dove ascoltare?

I podcast nell'app Replaio Radio In arrivo

I podcast stanno per arrivare nell'app. Installala ora e scopri per primo un modo tutto nuovo di vivere i podcast

Scaricala su Google Play Installala gratis Android quasi 10 mln di download · valutazione 4,8 iOS in arrivo

Episodi

አሁን ምን ያደርጋል የሴት ወየው ባይ፣ ወሎ የመጣው ሞት ሸዋ የለም ወይ? 14.12.2021

Leoul zewelde | Podcaster : Yeab Dems ምክንያት ይሰጡት እንጂ ፥ ሞት አይቀርም ። ተዘጋጅተው አይጠብቁት ነገር ደግLምክንያትዳ እንጂ ሙሽራ አይደለም ። በጦርነት ግፎች እንደሚሞት ሁሉ በሰላም ውስጥ ተኹኖም ይሞታል ። በረሃብ አረንቋ እንደሚሞት ፥ በጥጋብና አለቅጥ ውፍረትም ይሞታል ። ኤሊያሶች አይደለን አንዳናርግ ፥ ሮሙለስ አይደለን አንሠወርም ። ለማን እንደራራው - ለማን እንደሳሳው ይተወናል ? በአንድ ወቅት የሸዋረጋ ምኒሊክ ፥ የንጉሥ ሚካኤል ባለቤት ፥ ከወሎ አገር መከተሟን ሸዋዎች አልወደዱም ነበር ። ይህ አለመውደዳቸው ከወሎና ሸዋ ባላንጣነት ፥ ማለትም ከልጅ እያሱ መፈንቀለ መንግስት ጋር ይገናኛል...

የ አ ረ መ ኔ ፡ ክ ር ስ ት ያ ኖ ች ፡ ዘ ር ፡ ማ ጥ ፋ ት 31.10.2021

በመካከለኛው ዘመን ፥ አውሮጳ ግሪጎሪ ፱ኛ የተባለ ድመት ጠል ጳጳስ ትቀባለች ። ይህ እብሪተኛ ሰው በትረ ሙሴውን በጨበጠ ማግስት በፀሊም ድመቶች ላይ የዘር ማጥፋት (*Pogrom) አወጀ ። ይሄ አሰቃቂ የእልቂት አዋጅ በድመታውያን ታሪክ በክርስትያኖች የተፈፀመባቸው ትልቁ በደል ነው ። ነገሩ የሆነው እንዲህ ነው ። ተራማጅ እንደሆነ በአንደበቱ የሚናገረው ጳጳስ የጵጵስና ማዕረጉን ያገኘው በልጅ እግሩ በሰማንያ ዕድሜው ነበር ። መንበሩን እንደተቀበለም እረፍት አጥቶ ቀኖናዎችን ያሻሽል ገባ ። መታተሩንና እረፍት ማጣቱን ያዩ ሮማውያን የለውጥ ሐዋርያቸው አድርገው ተቀበሉት ። ለፍቅርና እምነት የተቀባው ጳጳስ ግን ነገረ ሥራው በየዓው...

የክብ መጨረሻ | Book: ጉራማይሌ 07.10.2021

የክብ መጨረሻ ፥ መጀመሪያው ነው ።

ያን ቀን ባታቆላምጪኝሥ? | ያልተላኩ አምስት መልዕክቶች ፥ መልዕክት - 2 23.09.2021

ያ ን ፡ ቀ ን ፥ ባ ታ ቆ ላ ም ጪ ኝ ስ ? [ ል ዑ ል ፡ ዘ ወ ል ደ ] ከወፍራም ብርጭቆ ላይ እያበረደች የምትቀምሰው ወተት የከንፈሯን ዳር በስልባቦት ይኩላል ። የአፏን ወተት ለመግፈፍ እጄን ሰድጄ ግልፋፊውን በጣቴ አስቀረሁ ። ያስቀረሁትን ቀመስኩ ። የላስኩትን ኬሚስትሪ ጣዕም ለማስረዳት ይቸግራል ። ሀይድሮጅን ደርድረው በቦንድ ቢስሉት ዘርፉ ከአሮጌ ዋርካ ይገዝፋል። ቤሎንዥ ፥ ዛሬ ንጋት ላይ ከፓሪስ-ቻርል የገባች ነው ። ስለሚደክም ፥ ችላ የምትመጣም አልመሰለኝም ነበር ። ለገሃር ሳባ ኬክ ቤት ተገናኘን ። ሳፊ ወተት ጋበዝኳት ። ግብዣው የይቅርታ ነው ። ከአምስት ቀን መዘጋጋት በኋላ የሀቅ ኩርፊያዬን ካድኩ ። ጥፋቱ...

ች ግ ራ ች ን ፡ ም ን ፡ ነ በ ር ? 16.09.2021

ሌላ ያልነገርኩሽ ፥ የልደትሽ ቀን አበባ ገዝቼ ነበር ። አዎ ! እኔ ። የሚገርምሽ ባገሩ እንደጠፋ ሁሉ የትናየት ሄጄ መሰለሽ ? መጨረሻ ላይ ወሰን ምናምን እሚሉት ሰፈር ትንሽዬ ኪዮስክ ውስጥ ትልቅ መቀስ የያዘች ሻጭ አየሁ ፤ ፈንታቸው መርገፍ የሆኑ ቅጠሎችን እየከረከመች። እንዲሁ ልጅ ሳለሁ ፥ ከትምህርት መልስ ሙሽራ የሚሉትን አበባ ከሰው አፀድ ቀጥፌ ወደቤቴ እሮጥልሻለሁ ። ቤት ልደርስ 'ከባቢ እጄ ከአበባው ተሻሽቶ ኖሮ ፥ ወየበ ። ከቆረጡት ኋላ ቶሎ የሚሞት አይነት ዘር ሆኖም ይሆናል ። ብቻ እጄ ላይ ከስሞ ፥ ነደደኝ ። የቀጠፍኩት እንዲያ እንዳማረበት ለ'ናቴ ልሰጣት ነበር ። ያም ሆኖ አልተውኩትም ። ከስራ መምጫዋን ጠብ...

Intala mootii 11.08.2021

አባት ሆይ … ! ፀልዬ አላውቅም - ብዙ እንዳትታዘበኝ ፤ ዛሬን ብቻ… ጆሮ ዳባ ሳትል … ለሥጋዬ ውሉድ ፥ አንዲት ማቲ ዋጀኝ ። 'ሴት' ሆና የማምናት ፤ ካለ ሚስት አለናት ፥ አባት 'ምሆናት ። አንዲት ልዕልት ማቲ ሳይጋሩኝ የምወዳት - ሳትጋራ የምትወደኝ አቤቱ - በረቂዮትህ ዋጀኝ ። ጡት ብነሳ እንደማልጋ ላም ባላግት ፥ ወተት ባላደማም ጀባ'ኝ እንጂ ፥ እንደ'ዶሮ ጭሬ አፀድቃታለው ህይወቴ የሷ መንግስት ነው ። አባት ሆይ … ፀልዬ አላውቅም - ብዙ እንዳትታዘበኝ ፤ ዛሬን ብቻ… ጆሮ ዳባ ሳትል … ለሥጋዬ ውሉድ ፥ አንዲት ማቲ ዋጀኝ ።

ዝ ም ታ ህ ን ፡ ማ ረ ኝ 04.08.2021

በያንዳንዱ የእምነት ክሬ እንደሹራብ ተተርትሬ እንዳልጣፍ እንዳልሰፋ ሆኛለው የቀረኝ ጨርቅ ከቅዳጄ ያነሰ ነው ። የሲዖል መልህቅ ከግሬ ታስሯል እፍግ ሰንሰለቱ እሄድኩት ድረስ ይረዝማል ቁርጭሚቴ ካልቦ ያለረፍት ይንቋቋል ህልው ምልክቴ ጠፍረ ባርያ ሆኗል ። * * * ቀደም . . .በሌት ግርማ ታውሬ ስቀይርህ ሳፈስህ ከደምስሬ በፋኑዔል ክንፍ ሰበዝ ደምቀለም ነክሬ ነብሴን ላውሬ ስቤዥ ዝም ብለኸኛል ! በካሚዮን ከሚንቦገቦገው በጥፍሮቹ ምድርን ቧጦ ከከበበው አይሆኑ ውዬ ለሌጊዮን ግዞት ስሸጥ በፊርማዬ ደግመህ ዝም ብለኸኛል ! በዚ ዝምታህ ዘላለምን ንቄ ቀቢፅ አፍታን ቃረምኩ ባይኖር ነው ብዬ ውድ ነብሴን ገበርኩ ። * * * ጌታዬ አ...

Excerpt : እና ፥ እየዘነበ ነው . . . 27.07.2021

ብዙ ግዜ እግሮቼን ይዞ የሚያስቀረኝን ማጥ የማቦካው እኔ ራሴው ነኝ ። ለዚህም ነው ድብርቴን ያመጣው ጭጋጉ ይሁን ጭጋጉ የመጣው በኔ ድብርት እርግጠኛ ያልሆንኩት ። በየግዜው የሚነሱብኝን ወጀቦችን እያሳለፍኩ እቆያለሁ - እኖራለሁ ለማለት እንኳ ትንሽ ይከብደኛል ። በአጭሩ ህይወቴ በረከት ርቋት ድንገት የሚወርድ ሲሳይ መጠበቅ ከጀመርኩ ቆየሁ ። ሰማዩ ገና ማስገምገም ሲጀምር ከጀርባዬ ያለውን መጋረጃ ለሁለት ከፍዬ ወደላይ አንጋጠጥኩ - ዳመናው ፅልመት አዝሏል ። አከታትሎ መብረቅ ወረደ ። ሁሌ አይቶ እንደማያውቅ ያስበረግገኛል ። ፀሃፊዬ " ድምፁ እኮ ዘግይቶ ነው የሚደርሰው ፤ መፍራት ያለብህ ብርሃኑን ነው " ስትለኝ ይሰማኛል ።...

'ወድሃለሁ ስትይ - ስሜቱን ግን ታውቂዋለሽ ? 09.04.2021

. . . ምልዓተዓለም ፀጥ እንደሚል ፤ ልቤ የምር እንደምትታፈን ፤ እግሬ እንደሚቀዳደም ፤ ብሌኖቼ እንደሚሰፉ ፤ ሳይታዘዝ ጉንጬ እንደሚፈግግ ፤ እየሄድኩ መቆም እንደሚያምረኝ ፤ እየቆምኩ መሄድ እንደሚያሰኘኝ ። ዝለል ዝለል እንደሚለኝ ፤ ሸራ ጫማዬን ፈትቼ እንደማስር ፤ ስልኬን አውጥቼ ሳልደውል መልሼ እንደምከተው ፤ ሽቶሽ ከየትም እንደሚሸተኝ ፤ የት መሄዱን ሳላውቅ ታክሲ እንደምሳፈር ፤ በውጥንቅጥ መሀል አንቺን ብቻ እንደማስብ ፤ የምጠላው ሙዚቃ እንደሚመስጠኝ ፤ አልፎ - ደንስ ደንስ እንደሚለኝ ። ሀይል ገላዬን እንደሚወር ፤ ደረቴ እንደሚረበሽ ፤ ላለፈ ለማኝ ሁሉ መቶ ብር ስጥ-ስጥ እንደሚለኝ ፤ በቀን እንደማልም ፤ ይለወ...

ታኂሬ- Bonus episode - Mar08. 08.03.2021

...

ለመውደቅ ግን ተሥፋ አለኝ • 07.03.2021

አንድ ልጇ ዱርዬ ሆኖ እንዳሸነፋት እናት … በካር ማህፀኗ ሌላ ዘር ሳይዝ … እሱኑ ስትል አሳድጋ… ሲያፄም ግዜ ከእጇ እንደወጣ… ደምላቧ ከንትቶ የምትኖርለት ሌላ ምክንያት እንዳጣች … ብዙ ብዙ ሄዶ እግዜርን ከቦታው እንዳጣ ቄስ … እድሜውን ሙሉ የቀራቸው መፃህፍት እርባን እንዳጡበት … ረፍዶ ከመመለስና ፣ ተሳስቶም ከመሄድ ምርጫ እንዳጣ … በሁለት የቂጡ ጉንጮች ሁለት ወንበር ላይ እንደተቀመጠ … … ተሥፋ አጥቻለው … አሳዳሪው አረጀህ ብሎ እንዳባረረው ውሻ ። እድሜ ዘመኑን በሳጥን ታጥሮ ኖሮ … ከግቢው ሲወጣ አቅም ከድቶት ቁጊያም እንደሆነ … የሰፈር ውሾች ሊነክሱ እንደሚያሳዱት … እድሜ ይፍታህ ታስሮ ድንገት በአመክሮ እንደ...

ጭንቀቴ መች ገባሽ 02.03.2021

…ጭንቀቴ… ድር እንዳጠመደው ዝንብ ነው ። ሸረሪቷ ካሁን አሁን መጣች እያለ እንደሚሳቀቅ … ክንፉን እያማታ… የትም እንደማይፈናፈን… …ጭንቀቴ…ለወር ታህል ቋጥራ እንደሚሾትልባት ነብሰጡር ነው ። ማህፀኗ አልረጋ እንዳላት … ዘጠኝ ወር ርቆ … የምልጃዋን ማርያም … ማርያም እንደምትል … ጭንቀቴ…ከእናት አባቱ ጥል አምልጦ እንደወጣ ህፃን ነው ። … የሚሮጥ መድረሻ የሌለው… ልጋጉን እየሳበ በለንባዳ አፉ እንደሚያለቅስ … …ጭንቀቴ … ፈረሰኞች በሌት መጥተው ጎተራውን እንዳነደደቡበት መጤ ነው ። ነጋጠባ ውጣልን እንደሚባል … ከአመድ ክምር ላይ ተቀምጦ… በለበቅ መሬት እንደሚጭር … …ጭንቀቴ… ደግመው ደጋግመው እንደደፈሯት ማቲ ነው...

•••ሥትናፍቂኝ 10.01.2021

ስ ት ና ፍ ቂ ኝ [ ል ዑ ል ፡ ዘ ወ ል ደ ] ስትናፍቂኝ … ባሏ ለዕድሜ ይፍታሕ ወህኒ እንደተወረወረባት ሴት ነው ። መልሳ ላታገኘው ነገር እሁድን እየጠበቀች እንደምትጠይቀው … ስትናፍቂኝ … ሲዖል ተኮራምቶ ገነትን እንደሚያልም ሠይጣን ነው ። ምህረት ሱሚ ሆኖበት በልቡ ማብከሪያ እንደሚለምን ። ጥፍሮቹን ቢከረክም'ም ርህራሄ ተነፍጎት ምናልባትን እንደያዘ… ስትናፍቂኝ … በምናብሽ የሚሄድ አስፋልት ሣይና በዛ ላይ በተቃራኒ አቅጣጫ የሚጓዝ ከንቱ ደሞ አስቢ ። እየሄደ የሚመስለው ግን አንድ ቦታ ላይ እንደቆመ ። ኃይሉ ሲሟጥ አስፋልቱ በራሱ አቅጣጫ እያንደባለለ እንደሚወስደው … ስትናፍቂኝ … ወደቀኝ እንደሚዞር ሽክርክር ሰዓት...

Ascolta il podcast Sost kilo su Replaio

Radio e podcast in un'unica app - gratis e senza registrazione. Installala oggi e non perderti il lancio

Scaricala su Google Play

Replaio non è un editore di podcast; i nomi dei programmi, le copertine e l'audio appartengono ai rispettivi autori e vengono distribuiti tramite feed RSS pubblici