ዶ/ር ቤንጃሚን ዲን

Great Truths Podcast (Amharic)

Arts EN ↓ 35 episodes

This is the Amharic version of the Great Truths Podcast. ይህ ፖድካስት የእግዚአብሔር ቃልን በተሻለ መንገድ ለመረዳት እና የመፅሐፍ ቅዱስን መልዕክት ዛሬ ለእኛ ምን እንደሆነ ለማወቅ ይረዳናል። ታላቅ እውነት (Great Truths) ለትርፍ ያልተቋቋመ፣ ከ 10 ሚሊዮን በላይ የሆኑ የወንጌል አማኝ መሪዎችን (መጋቢዎች፣ እረኞች፣ ቄሶች፣ ሰባኪዎች፣ እና ወንጌላውያኖችን) ለማገልገል የሚፈልግ፣ ደግሞም በአለማችን ያሉ 660 ሚሊዮን ወንጌል አማኝ ክርስትያኖችን ከፍተኛ ጥራት ባላቸው የሚዲያ አማራጮች መፅሐፍ ቅዱስን ለማስተማር የሚሻ ተቋም ነው። ለበለጠ መረጃ እና የእያንዳንዱን ምዕራፍ ሙሉ መፅሐፍ ከተጨማሪ ግብዐቶች ጋር ለማግኘት ድህረ ገፃችንን ይመልከቱ https://amharic.greattruthsglobal.org/  

Author

ዶ/ር ቤንጃሚን ዲን

Category

Arts

Latest episode

Jan 26, 2026

Where to listen?

Podcasts in the app Replaio Radio Coming soon

Podcasts are coming to the app soon. Install now and be the first to see a whole new take on podcasts

Get it on Google Play Install for free Android 5M+ downloads · 4.8 rating iOS soon

Episodes

የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ #10 | የኢየሱስ ትንሣኤ እውነተኝነት (ክፍል 1) 15.04.2025

የክርስቶስ ትንሣኤ የተለመዱ ታሪካዊ ክሥተቶችንና የተፈጥሮ ሕጎችን ሁሉ ዐልፎ የሚሄድ ታሪካዊ እውነት ነው። ሁሉን ቻዩ እግዚአብሔር የተለመዱ ተፈጥሯዊ ሕጎችንና ደንቦችን በሙሉ በመጣስ በክርስቶስ ትንሣኤ ድንቅ ተኣምራዊ ሥራውን ሠርቷል። የክርስቶስ ትንሣኤ ከሰዎች ጥበብና መረዳት፣ እንዲሁም ከተፈጥሮ ሂደት በላይ የሆነ ክሥተት ነው። በተጨማሪም ክሥተቱ ከእግዚአብሔር የማዳንና ፍጥረትን የማደስ ሥራ ጋራ የተቆራኘ ነው። 

የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ #9 | ትንሣኤ ሁሉን ቻይነትን መሠረት ያደረገ ነው (ክፍል 2) 08.04.2025

የክርስቶስ ትንሣኤ የእምነታችንን ቁልፍ ስፍራ ይይዛል። በክርስቶስ ትንሣኤ ሞት ማመናችን በእግዚአብሔር መታመናችንና በርሱ መተማመናችንን የሚያረጋግጥ ልዩ መገለጫ ነው። ያለ ክርስቶስ ትንሣኤ ክርስቲያናዊ ትምህርቶች ምንነትና ትርጒም አይኖራቸውም። ክርስቶስንም ሆነ የአማኝን ተስፋ ያለ ኢየሱስ አካላዊ ትንሣኤ ለማወጅ መጣር፣ የእምነትን መሠረታዊ እውነት ወደ ሚንድ ደረጃ የሚያደርስ ነገር ሲሆን የክርስቶስ ወንጌል የሞቱና የትንሣኤው ወንጌል ነው። 

የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ #8 | ትንሣኤ ሁሉን ቻይነትን መሠረት ያደረገ ነው (ክፍል 1) 25.03.2025

የክርስቶስ ትንሣኤ የእምነታችንን ቁልፍ ስፍራ ይይዛል። በክርስቶስ ትንሣኤ ሞት ማመናችን በእግዚአብሔር መታመናችንና በርሱ መተማመናችንን የሚያረጋግጥ ልዩ መገለጫ ነው። ያለ ክርስቶስ ትንሣኤ ክርስቲያናዊ ትምህርቶች ምንነትና ትርጒም አይኖራቸውም። ክርስቶስንም ሆነ የአማኝን ተስፋ ያለ ኢየሱስ አካላዊ ትንሣኤ ለማወጅ መጣር፣ የእምነትን መሠረታዊ እውነት ወደ ሚንድ ደረጃ የሚያደርስ ነገር ሲሆን የክርስቶስ ወንጌል የሞቱና የትንሣኤው ወንጌል ነው። 

የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ #7 | የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ባሕርይ (ክፍል 2) 21.03.2025

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ፣ ግልጽ ያልሆነ ስውር ምስጢር ወይም በንግግር ደረጃ ብቻ ሊገለጽ የሚቻል ነገር ሳይሆን፣ በእውን የተደረገ አካላዊና ታሪካዊ ሀቅ ነው። ትንሣኤው በተግባር የተከናወነ፣ በበርካቶች በስፋት የተመሰከረ፣ ለብዙዎች ፊት ለፊት የታየና እውነት ስለ መሆኑ የተረጋገጠ ክሥተት ነው። የክርስቶስ ትንሣኤ ከታሪካዊ እውንነቱም በላይ፣ የርሱን መለኮታዊ ኀይል ከወቅታዊው ታሪካዊ ክሥተት ጋራ አቆራኝቶ የሚያሳይ ነው።

የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ #5 | የትንሣኤ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትንበያና ታሪካዊ ዳራ (ክፍል 2) 16.03.2025

በሉቃስ 24፥26-27 ባለው ክፍል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በርሱ ላይ ሊደርስ ስላለው መከራና ሥቃይ፣ እንዲሁም ከዚያ በኋላ ሊሆን ስላለው ክብር ተግባራዊነትና አስፈላጊነት በሙሴ፣ በነቢያትና በመጻሕፍት ሁሉ አስቀድሞ ስለመነገሩ ከትንሣኤው በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ተናግሮ ነበር። 

የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ #6 | የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ባሕርይ (ክፍል 1) 16.03.2025

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ፣ ግልጽ ያልሆነ ስውር ምስጢር ወይም በንግግር ደረጃ ብቻ ሊገለጽ የሚቻል ነገር ሳይሆን፣ በእውን የተደረገ አካላዊና ታሪካዊ ሀቅ ነው። ትንሣኤው በተግባር የተከናወነ፣ በበርካቶች በስፋት የተመሰከረ፣ ለብዙዎች ፊት ለፊት የታየና እውነት ስለ መሆኑ የተረጋገጠ ክሥተት ነው። የክርስቶስ ትንሣኤ ከታሪካዊ እውንነቱም በላይ፣ የርሱን መለኮታዊ ኀይል ከወቅታዊው ታሪካዊ ክሥተት ጋራ አቆራኝቶ የሚያሳይ ነው። 

የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ #1 | የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የእግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድ እና የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሥራ ነው 15.02.2025

የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ ታሪክ በከፍተኛ ደረጃ የተገለጠ ተኣምራዊ ክሥተት ሲሆን፣ አስፈላጊነቱና ጥቅሙም እጅግ ከፍ ያለ ነው። ይህም ሊሆን የቻለው በአንድ አገር ወይም አህጉር ብቻ በተወሰነ መልኩ ሳይሆን፣ የክርስቶስን ማንነት የሰው ልጆችን ምንነት፣ የፍጥረታትን ሁኔታ እና የሰማይንና የምድርን አፈጣጠር ሁሉ ባጠቃለለ መልኩ ትርጉም ሊሰጥ በሚችልበት መንገድ ነበር። በዚህ ፖድካስት እንደምንመለከትው ክርስቶስ ራሱና የአዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች የክርስቶስ ትንሣኤ፣ ክርስቶስ የራሱን መለኮታዊ እና ሰብአዊ ማንነቱንና ያሳካቸውን ተግባራት በሙሉ በትንሣኤው ኀይሉ እንዳረጋገጠ እንገነዘባለን። 

የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ #2 | ሞቱ ትንሣኤውን ይቀድማል 15.02.2025

የክርስቶስ ኢየሱስ ትንሣኤ ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ላይ የነበረው ሕይወቱና አገልግሎቱ ማብቂያ ያገኘበት ክሥተት ስለመሆኑ ከወንጌላት ዘገባ መረዳት እንችላለን። በአጠቃላይ መልኩ ሲታይ የዚህ እውነት ታሪካዊ ዳራውና ቀጥተኛ ዐውዱ የሰው ልጆች ሁሉ ሞት ሲሆን፣ በተለየ መልኩ ደግሞ የኢየሱስ ክርስቶስ ሞት ነው። የክርስቶስ ኢየሱስ ሞት የሰውን ልጆች ክፋትና ዐመፀ ጥግ የሚያሳይ ሲሆን፣ በሌላ ጎኑ ሲታይ ደግሞ የክርስቶስ መስቀል የሚያሳየው በሰዎች ኀጢአትና ዐመፅ ላይ የተገለጠውን የእግዚአብሔርን ፍትሓዊ ፍርድ ነው።  

የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ #3 | የክርስቶስ ትንሣኤ ቀዳማዊ አስፈላጊነት 15.02.2025

የክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ የማይነጣጠሉ መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነቶች፣ እንዲሁም የወንጌል መሠረትና ማእከል ቢሆኑም፣ ትንሣኤው ግን ቁልፍ ክሥተት ነው። ምክንያቱ ደግሞ ክርስቶስ በሕይወቱና በሞቱ የሠራቸው ነገሮች በሙሉ ግልጽ በሆነ መልኩ የሚታዪቱና በአማኞች ሕይወት ላይ ተግባራዊ ሊደረጉ የሚችሉት በክርስቶስ የትንሣኤ አካል አማካኝነት ስለሆነ ነው። በመሆኑም፣ ትንሣኤ የሁሉም ነገር መሠረትና ማእከል ሲሆን፣ የክርስትና እምነት የመሠረት ድንጋይም ጭምር ነው። 

የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ #4 | የትንሣኤ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትንበያና ታሪካዊ ዳራ (ክፍል 1) 15.02.2025

በሉቃስ 24፥26-27 ባለው ክፍል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በርሱ ላይ ሊደርስ ስላለው መከራና ሥቃይ፣ እንዲሁም ከዚያ በኋላ ሊሆን ስላለው ክብር ተግባራዊነትና አስፈላጊነት በሙሴ፣ በነቢያትና በመጻሕፍት ሁሉ አስቀድሞ ስለመነገሩ ከትንሣኤው በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ተናግሮ ነበር። 

Listen to the Great Truths Podcast (Amharic) podcast in Replaio

Radio and podcasts in one app - free, with no sign-up. Install today and do not miss the launch

Get it on Google Play

Replaio is not a podcast publisher; show names, artwork and audio belong to their authors and are distributed through public RSS feeds.